የኢንዱስትሪ እና የማዕድን ልማት ጉዳዮች
የኢንዱስትሪ እና የማዕድን ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሚከተሉት ጉዳዮች ላይ ክትትልና ቁጥጥር ያከናውናል፡-
1/ የኢንዱስትሪ በተለይም የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ልማትንና ተወዳዳሪነትን በቀጣይነት የሚያረጋግጡ ፖሊሲዎችን፣ ስትራቴጂዎችንና ህጎች መቀረፃቸውን፤ አፈጻጸሙ ከሀገራዊ የልማት አቅጣጫ ጋር የተጣጣመ ዝርዝር መርኃ ግብር መዘጋጀቱ እና ተግባራዊ አፈፃፀሙ፤
2/ በኢንዱስትሪ በተለይም በማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ዘርፍ የግል ዘርፉን ተሳትፎና ሚና ለማሳደግ የሚያስችል ሥርዓት መዘ,ርጋቱ፤
3/ በኢንዱስትሪ በተለይም ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ልማት ትኩረት የሚሠጣቸውን ጨርቃ ጨርቅ፣ ቆዳ እና የምግብና መጠጥ እንደስትሪዎችና የመሳሰሉት ንዑስ ዘርፎች ካላቸው አንጻራዊ ጠቀሜታና እምቅ አቅም አኳያ መለየታቸውንና አፈጻጸሙ ዝርዝር ከሀገራዊ የልማት አቅጣጫ ጋር የተጣጣመ መርኃ ግብር መዘጋጀቱ እና ተግባራዊ መደረጉን፤
4/ በዘርፉ ምርምርና ጥናት የሚያካሂዱ አካላትን አስፈላጊዉን ድጋፍ በማድረግ የኢንዱስትሪዎችን፣ የኢንቨስትመንት እና የማኑፋክቸሪንግ አቅምና ተወዳዳሪነትን እንዲያድግ መደረጉን፤
5/ በኢንቨስትመንት ህግ መሠረት የሀገር ውስጥ እና የውጭ ባለሃብቶች በማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ዘርፍ ኢንቨስትመንት የሚሳተፉበትን ሁኔታዎች መመቻቸቱን በሥሩ ያሉ ተጠሪ ተቋማት በዋናነት ለሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ድጋፍ እንዲሰጡ ለማድረግ ተገቢውን ሥርዓት መዘርጋቱንና ውጤታማነቱ፤
6/ የኢንዱስትሪ በተለይም የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ዘርፍ ልማትና ምርታማነትን ለማሳደግ ኢንዱስትሪዎች የኤክስቴሽን አገልግሎት፣ የቴክኖሎጂ፣ የግብዓትና የግብይት እንዲሁም በአመራረት ረገድ ድጋፍ እንዲያገኙ መደረጉን፤
7/ የኢንዱስትሪ በተለይም የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ምርቶች የጥራት ደረጃቸውን የጠበቁ፣ በዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የአቅም ግንባታ፣ የምርምርና ስርጸት ሥራዎች እንዲከናወኑ ሥርዓት መዘርጋቱን እና ተግባራዊ አፈፃፀሙን፤
8/ ኢንዱስትሪንና ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋት የሚያበረታቱ ተግባራት በአግባቡ እየተከናወኑ መሆናቸውን፤
9/ ስትራቴጂያዊ ትኩረት ለሚሠጣቸው ኢንዱስትሪዎች ተገቢው ድጋፍ እየተሠጠ መሆኑን፤
10/ የኢንዱስትሪ ልማትን ለማፋጠን የሚያስችሉ እና ለኢንቨስትመንት የተመቻቹ ህጐች፣ ፓሊሲዎችና ስትራቴጂዎች መኖራቸው እና በአግባቡ በሥራ ላይ መዋላቸውን፤
11/ አነስተኛና መካከለኛ ተቋማት ልማትን ለማስፋፋት የሚደረገው እንቅስቃሴ፤
12/ ለኢንዱስትሪዎች አስተማማኝ ግብዓት ለማቅረብ የሚያስችል ስልት መቀየሱን እና የግብዓት አቅርቦት ትስስር ስርዓት መዘርጋቱን፤
13/ በአነስተኛ፣ በመካከለኛና በከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች መካከል የተቀናጀ ትስስር እንዲፈጠር የሚያስችል ስርዓት መዘርጋቱን እንዲሁም አነስተኛ ኢንዱስትሪዎች ወደ መካከለኛና ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች እንዲሸጋገሩ አስፈላጊው ድጋፍ መሰጠቱን፤
14/ የኢንዱስትሪ የዘርፍና የሙያ ማህበራት እንዲቋቋሙና ጠንክረው እንዲንቀሳቀሱ የሚደረገውን ማበረታቻ፤
15/ ኢንቨስትመንት የመሳብ፣ ለባለሃብቶች ምቹ እና ቀልጣፋ አሰራር እና ስርዓት መፈጠሩን፣ ባለሃብቶችን ወደ ስራ የማስገባት እንዲሁም ከኢንቨስትመንት የሚገኘውን ሁሉን አቀፍ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ረገድ የሚከናወኑ ተግባራትን ውጤታማነትን፤
16/ የማዕድን፣ የጂኦተርማል፣ ነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ ልማትን የሚመለከቱ ፓሊሲዎችን፣ ስትራቴጂዎችንና የሕግ ማዕቀፍ መቀረፁን፤ ለአፈጻጸሙ ከሀገራዊ የልማት አቅጣጫ ጋር የተጣጣመ ዝርዝር መርኃ ግብር መዘጋጀቱን እና ወደ ተግባር መግባቱን፤
17/ የማዕድን፣ ነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ ፍለጋንና የሥነ-ምድር መረጃዎች መደራጀታቸውን፤ መረጃዎችን ለኢንቨስትመንትና ለልማት ተደራሽ መደረጉን፤
18/ የማዕድን፣ ነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ ልማት ሥራዎችን ለማፋጠን የሚውሉ የቤተሙከራና የማዕድን ጥራት ማረጋገጫ ማዕከላትን እንዲሁም የምርምርና የማሰልጠኛ ተቋማትን መደራጀታቸውን፤
19/ የማዕድን፣ የነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ ኢንቨስትመንትና ልማት የግል ዘርፉ ተሳትፎና ሚናን ለማሳደግ የሚያስችል የአሰራር ሥርዓት መዘርጋቱን እና ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን፤
20/ የማዕድን፣ የነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ ምርት ፍለጋን እና ምርቱን ወደ ገበያ ለማሸጋገር የሚያስችል ዘመናዊ አሠራሮችን መዘርጋቱን፤
21/ በማዕድን፣ በነዳጅና በተፈጥሮ ጋዝ ፍለጋና ልማት ለሚሰማሩ ባለሃብቶች ምቹ ሁኔታ መፈጠሩንና ግዴታቸውንም በገቡት ውል መሠረት እንዲፈጽሙ የሚደረገውን እንቅስቃሴ፤
22/ የማዕድን፣ የነዳጅና የተፈጥሮ ጋዝ ልማት መስፋፋቱንና መረጃዎች በአግባቡ ተደራጅተው ለአገልግሎት ዝግጁ መደረጋቸውን፤
23/ የተፈጥሮ ጋዝና የነዳጅ ምርቶች የጥራት ደረጃ መረጋገጡንና የማከማቻና ማከፋፈያ ተቋማት ደረጃ አሰጣጥ በአግባቡ መከናወኑን፤
24/ የአገሪቷ የተፈጥሮ ሃብት አጠቃቀም የዘላቂ ልማት መርሆዎችን በተከተለ አግባብ መሆኑን፤
25/ የሚከታተላቸውና የሚቆጣጠራቸው ተቋማትን የሚመለከቱ ፖሊሲዎች፣ ህጎች፣ ስትራቴጂዎች እና ዕቅዶች በአግባቡ በሥራ ላይ መዋላቸውን፤
26/ የሚከታተላቸውና የሚቆጣጠራቸው ተቋማት የተመደበላቸውን በጀት በአግባቡና በውጤታማነት በስራ ላይ ማዋላቸውን ፡፡