የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢ እና አካባቢ ጥበቃ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ

የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢ እና አካባቢ ጥበቃ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ተግባር እና ኃላፊነት

ውሃ፣ መስኖ ቆላማ አካባቢ እና አካባቢ ጥበቃ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሚከተሉት ጉዳዮች ላይ ክትትልና ቁጥጥር ያከናውናል፡-

1/   ውሃና ኢነርጂን የሚመለከቱ ፖሊሲዎችን፣ ስትራቴጂዎችን እና ህጎችን መቀረፃቸውን አፈጻጸሙ ከሀገራዊ የልማት አቅጣጫ ጋር የተጣጣመ መሆኑን፤

2/  የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደርን በተፋሰሶች ውስጥ ተግባራዊ ከማድረግ አኳያ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር የሚረዱ የፖሊሲ ጥናቶችን፣ ቅኝቶችንና ምርምሮችን መደረጋቸውንና መፈፀማቸውን፤

3/   በተፋሰሶች ውስጥ የሚተገበሩ ከውሃ ጋር የተገናኙ ፕሮጀክቶችና እንቅስቃሴዎች ከተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር ሂደቶችውሃ ሀብት ስትራቴጂክ እቅድ እና ተግባራትን ለመምራትና ለመደገፍ የሚያስችል የተፋሰስ ሞዴል መዘርጋቱን፤

4/  የአገሪቱን የከርሰ ምድርና ገጸ ምድር የውሃ ሀብት በመጠንና በጥራት ጥቅም ላይ የሚውልበትን ሁኔታ መመቻቸቱን፤ በውሀ አጠቃቀም ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብሮችን መቀረፃቸውንና ተግባራዊ መደረጉን፤

5/  ፍትሃዊ የውሃ አጠቃቀምን ለማስፈን የሚያግዝ ዘላቂ እና የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር ሥርዓት መፈጠሩን፤

6/  የውሃ ሃብት፣ የአካባቢ ጥበቃ ልማትና አጠቃቀምን አቅርቦት እድገትና ስርጭትን

7/  የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ሽፋን እንዲያድግ እገዛ መደረጉን ፣ የአማራጭ ኢነርጂ ምንጮችና ቴክኖሎጂዎች ልማት እንዲስፋፋ መደረጉን እና የመካከለኛና ከፍተኛ መስኖ ልማት ለማስፋፋት የሚያስችሉ የጥናት፣ የዲዛይን እና የግንባታ ሥራዎች በአግባቡ መከናወናቸውን

8/  የሜቲዎሮሎጂ አገልግሎት ሥራ በአግባቡ መከናወኑን፣ እና ለአገሪቱ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት አስተዋፆ እያበረከተ መሆኑን፤

9/  የሀገሪቱ የተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀም ለዘላቂ ልማት መርሆችን በተከተለ አግባብ መሆኑ፤

10/ የአካባቢ ደህንነትና ጥበቃ ዓላማዎችና ፖሊሲዎች በስራ ላይ መዋላቸውንና ውጤታማነታቸው መረጋገጡን፤

11/ የልማት ፕሮጀክቶችና ፕሮግራሞች በአካባቢ ተፅኖ ግምገማ ስርዓት መሰረት ተግባራዊ መሆናቸው፤

12/ የመስኖ ልማት፣ የቆላማ፣ እና ለድርቅ ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎች እና የአርብቶ አደር ልማትን የሚመለከቱ ፖሊሲዎችን፣ ስትራቴጂዎች፣ ህጎች መዘጋጀታቸውን፣ አፈጻጸሙ ከሀገራዊ የልማት አቅጣጫ ጋር የተጣጣሙ መሆናቸውን፤

13/ የመስኖ ልማት መስፋፋታቸውን፤

14/ የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶችን ምርታማነት በሚያሳድጉ ወቅታዊ ቴክኖሎጂዎች መደገፋቸውንና ውሃ ቆጣቢ አሠራር መከተላቸውን፤ 

15/ በተቀናጀ የተፋሰስ ልማት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ጥናት የተለዩ የሀገሪቱን የከርሰ ምድር እና የገፀ ምድር የውሃ ሃብት ለመስኖ ልማት መዋላቸውን፤

16/ የመስኖ ልማት ሽፋን እንዲያድግ የሚያደርግ የአሠራር ሥርዓት መዘርጋቱን፤

17/ በመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች የአካባቢው ህብረተሰብ ተሳታፊና ተጠቃሚ መሆናቸውን፤

18/ በቆላ አካባቢዎች ያለውን የመስኖ ልማት አቅም የአካባቢውን የግብርና መሬት ለማልማት የሚያስችል የመስኖ ልማት ፕሮግራሞችን መቀረፁን፤

19/ አርብቶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች የማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት መከናወናቸውን፤

20/ የሚከታተላቸውና የሚቆጣጠራቸው ተቋማትን የሚመለከቱ ፖሊሲዎች፣ ህጎች፣ ስትራቴጂዎች እና እቅዶች በአግባቡ በሥራ ላይ መዋላቸውን፤

21/ የሚከታተላቸውና የሚቆጣጠራቸው ተቋማት የተመደበላቸውን በጀት በአግባቡና በውጤታማነት በስራ ላይ ማዋላቸውን፡፡

የኮሚቴው ሰብሳቢዎች

የኮሚቴው ሪፖርት

የኮሚቴው አባላት