እቅድ፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች
የኘላን፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሚከተሉት ጉዳዮች ላይ ክትትልና ቁጥጥር ያከናውናል፡-
1/ የልማት፣ የሀገራዊ የስታቲስቲክስ፣ የሥነ-ህዝብ፣ የአየር ንብረት ለውጥንና አካባቢን የሚመለከቱ ፖሊሲዎች፣ ስትራቴጂዎችና ህጎችን መዘጋጀታቸውን፣ አፈጻጸሙ ከሀገራዊ የልማት አቅጣጫ ጋር የተጣጣመ ዝርዝር መርኃ ግብር መዘጋጀቱን እና ተግባራዊነቱን፤
2/ አገራዊ የረጅም ዘመን አመላካች የልማት ፕላን መዘጋጀቱን፣ የአገሪቱን የአጭርና የመካከለኛ ዘመን የልማት ፕላንና ፕሮግራም ሥራ ላይ መዋሉን፤
3/ የልማት ፕላን አካል የሆነውን አገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገት ትንበያና የማክሮ ኢኮኖሚ ማዕቀፍ መዘጋጀቱን፤ ከማክሮ ኢኮኖሚ ማዕቀፉ የተጣጣሙ የቁጠባ፣ የኢንቨስትመንት እና የወጪና የገቢ ንግድ የማክሮ ኢኮኖሚ ግቦችን መውጣታቸውን፤
4/ በመላ አገሪቱ የተመጣጠነ ልማት እና ውጤታማ የመሬት አጠቃቀምን ለማሳካት ሀገራዊ የስፓሻል ፕላን መዘጋጀቱን እና ተባራዊነቱን፤
5/ የክልሎችንና የዜጎችን ፍትሐዊ የመልማትና የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያግዝ ሥርዓት መዘርጋቱን፤
6/ የፖሊሲ ጥናትና ምርምር ስራዎችን መከናወናቸውን፤
7/ የልማት ፕላንን ለማሳካት እንዲሁም የመንግስት የማስፈፀም አቅም ለማጠናከርና ቀጣይነት ያለው ተቋማዊ አቅም እንዲፈጠር የአስፈፃሚ ተቋማት ሪፎርም እና የሥርዓት ማሻሻያ ጥናት መካሄዳቸውን፤ እና አተገባበሩ፤
8/ ለፊስካል በተለይም ለታክስና ለቀረጥ ሕጎች መሠረት የሚሆኑ ፖሊሲዎችን፣ ስትራቴጂዎችና ህጎች መቀረፃቸውን፣ አፈጻጸሙ ዝርዝር ከሀገራዊ የልማት አቅጣጫ ጋር የተጣጣመ መርኃ ግብር መዘጋጀቱን እና ተግባር ላይ መዋሉን፤
9/ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የፌደራል መንግሥትን የበጀት፣ የሂሣብ አያያዝ፣ የክፍያና የውስጥ ኦዲት ሥርዓት መዘርጋቱን፤ አፈጻጸሙን ውጤታማነቱን፤
10/ የፌደራል መንግስት እና የክልል መስተዳድር የበጀት፣ የሂሣብ አያያዝ፣ የክፍያና የውስጥ ኦዲት ሥርዓቶች አንድ ወጥና የተጣጣሙ መሆናቸውን፤
11/ የፌደራል መንግሥቱን የግዢና የንብረት አስተዳደር ሥርዓት መዘርጋቱንና የአፈጻጸም ውጤታማነት፤
12/ የፌደራል መንግሥት አክሲዮኖችን፣ የሚተላለፉና የማይተላለፉ የገንዘብ ሰነዶችንና ሌሎች ተመሳሳይ ተቀማጭ የገንዘብ ሀብቶችን መያዙን እና የተለያዩ ፈንዶችን ለታለመላቸው ዓላማ መዋላቸውን፤
13/ የፌደራል መንግስት ፋይናንስ እና ንብረት አስተዳደር በአግባቡ መከናወኑን እና ውጤታማ መሆኑን፤
14/ የአገሪቱን የኢኮኖሚ ዕድገት ቀጣይነት እና ፍትሃዊነት እንዲሁም የተረጋጋ የማክሮ - ኢኮኖሚ ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ፓሊሲዎች መመንጨታቸውን እና በአግባቡ ስራ ላይ መዋላቸውን፣ ኢኮኖሚው በተገቢው መንገድ እየተመራ መሆኑን፤
15/ የአገሪቱ የልማት እቅድ እና የልማት ፕሮጀክቶች የአዘገጃጀትና አፈፃፀም ስርዓት መዘርጋቱን እንዲሁም በወቅቱ በስራ ላይ መዋሉን፤
16/ ለክልሎች የሚሰጥ ድጎማ በቀመሩ መሠረት መጽደቁን፤
17/ የአገሪቱ የስነ-ህዝብ ፓሊሲ መዘጋጀቱን፣ የማክሮ - ኢኮኖሚና የፊስካል ፖሊሲዎች መመንጨታቸውን እና በትክክል በስራ ላይ መዋላቸውን፤
18/ የኢኮኖሚ ትብብሮችና ትስስሮች ከመደረጋቸው በፊት በአገሪቱ የኢኮኖሚ አፈፃፀም ላይ የሚያስከትሉት ውጤት የሚፈተሽ እና የሚገመገም መሆኑን፤
19/ የፌደራል መንግሥት ዓመታዊ በጀት በአግባቡ ተዘጋጅቶ መቅረቡን እና መጽደቁን፤
20/ የአገሪቱ የገንዘብ እና የኢኮኖሚ ልማትና ትብብር ተግባራት በአግባቡ እየተከናወኑ መሆናቸውን፤
21/ የፌደራል መንግስት ታክስና ቀረጥ አስተዳደር እንዲሁም የመንግስት ገቢ አሰባሰብ በአግባቡ እየተከናወነ መሆኑን፤
22/ ትክክለኛ የሆነ የመንግስት የበጀት፣ የሂሳብ አያያዝ፣ የክፍያና የውስጥ ኦዲት ስርዓት መዘርጋቱንና በአግባቡ እየተፈፀመ መሆኑን፤
23/ በመንግስት የኢኮኖሚና የፋይናንስ ፖሊሲ መሠረት የመንግስት የልማት ድርጅቶች በአገሪቱ የኢኮኖሚና ንግድ እንቅስቃሴ ገንቢ ሚና እያበረከቱ መሆኑን፤
24/ የፌዴራል አገር ውስጥ ገቢ አፈጻጸም ለማሻሻል እና ገቢ በአግባቡ እንዲሰበሰብ ለማድረግ ስትራቴጅዎችን መቅረፁን እና የአሰራር ስርአት መዘርጋቱን፤
25/ የፌዴራል አገር ውስጥ ገቢ የመሰብሰብ አቅም ግንባታን በቀጣይነት የሚያረጋግጡ አሠራሮችን መቀረፃቸውን እና አተገባበራቸውን፤
26/ ዘመናዊ የአገር ውስጥ ገቢ አወሳሰንና አሰባሰብ ሥርዓት መዘርጋቱንና ተግባራዊነቱን፤
27/ ታክስ ከፋዮች በፍቃደኝነት ታክስ የመክፈል ባሕልን እንዲያዳብሩ የሚያግዝ ስርዓት መዘርጋቱንና ተግባራዊ አፈፃፀሙን፤
28/ ለክልል የገቢ ሰብሳቢ አካላት ተገቢውን የአቅም ግንባታ ድጋፍ መስጠቱን፣ የፌደራልና የክልል ታክስ አስተዳደር ሥርዓት የሚጣጣሙበትን ሁኔታ መፍጠሩን፤
29/ የመንግስት የልማት ድርጅቶች የስራ እንቅስቃሴ የገበያ ጉድለትን የሚሞላ እና የነፃ ገበያ ኢኮኖሚ ግንባታን የሚደግፍ እንዲሁም ትርፋማነትና የቴክኖሎጂ ሽግግርን የሚያረጋግጥ መሆኑን፤
30/ የሚከታተላቸውና የሚቆጣጠራቸው ተቋማትን የሚመለከቱ ፖሊሲዎች፣ ህጎች፣ ስትራቴጂዎች እና እቅዶች በአግባቡ በሥራ ላይ መዋላቸውን፤
31/ የሚከታተላቸውና የሚቆጣጠራቸው ተቋማት የተመደበላቸውን በጀት በአግባቡና በውጤታማነት በስራ ላይ ማዋላቸውን፡፡