እቅድ፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች

የኘላን፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሚከተሉት ጉዳዮች ላይ ክትትልና ቁጥጥር ያከናውናል፡-

1/    የልማት፣ የሀገራዊ የስታቲስቲክስ፣ የሥነ-ህዝብ፣ የአየር ንብረት ለውጥንና አካባቢን የሚመለከቱ ፖሊሲዎች፣ ስትራቴጂዎችና ህጎችን መዘጋጀታቸውን፣ አፈጻጸሙ ከሀገራዊ የልማት አቅጣጫ ጋር የተጣጣመ ዝርዝር መርኃ ግብር መዘጋጀቱን እና ተግባራዊነቱን፤

2/    አገራዊ የረጅም ዘመን አመላካች የልማት ፕላን መዘጋጀቱን የአገሪቱን የአጭርና የመካከለኛ ዘመን የልማት ፕላንና ፕሮግራም ሥራ ላይ መዋሉን፤

3/    የልማት ፕላን አካል የሆነውን አገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገት ትንበያና የማክሮ ኢኮኖሚ ማዕቀፍ መዘጋጀቱን፤ ከማክሮ ኢኮኖሚ ማዕቀፉ የተጣጣሙ የቁጠባ፣ የኢንቨስትመንት እና የወጪና የገቢ ንግድ የማክሮ ኢኮኖሚ ግቦችን መውጣታቸውን፤ 

4/    በመላ አገሪቱ የተመጣጠነ ልማት እና ውጤታማ የመሬት አጠቃቀምን ለማሳካት ሀገራዊ የስፓሻል ፕላን መዘጋጀቱን እና ተባራዊነቱን፤

5/    የክልሎችንና የዜጎችን ፍትሐዊ የመልማትና የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያግዝ ሥርዓት መዘርጋቱን፤

6/    የፖሊሲ ጥናትና ምርምር ስራዎችን መከናወናቸውን፤

7/    የልማት ፕላንን ለማሳካት እንዲሁም የመንግስት የማስፈፀም አቅም ለማጠናከርና ቀጣይነት ያለው ተቋማዊ አቅም እንዲፈጠር የአስፈፃሚ ተቋማት ሪፎርም እና የሥርዓት ማሻሻያ ጥናት መካሄዳቸውን፤ እና አተገባበሩ፤

8/    ለፊስካል በተለይም ለታክስና ለቀረጥ ሕጎች መሠረት የሚሆኑ ፖሊሲዎችን፣ ስትራቴጂዎችና ህጎች መቀረፃቸውን፣ አፈጻጸሙ ዝርዝር ከሀገራዊ የልማት አቅጣጫ ጋር የተጣጣመ መርኃ ግብር መዘጋጀቱን እና ተግባር ላይ መዋሉን፤

9/     ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የፌደራል መንግሥትን የበጀት፣ የሂሣብ አያያዝ፣ የክፍያና የውስጥ ኦዲት ሥርዓት መዘርጋቱን፤ አፈጻጸሙን ውጤታማነቱን

10/  የፌደራል መንግስት እና የክልል መስተዳድር የበጀት፣ የሂሣብ አያያዝ፣ የክፍያና የውስጥ ኦዲት ሥርዓቶች አንድ ወጥና የተጣጣሙ መሆናቸውን፤

11/  የፌደራል መንግሥቱን የግዢና የንብረት አስተዳደር ሥርዓት መዘርጋቱንና የአፈጻጸም ውጤታማነት፤

12/  የፌደራል መንግሥት አክሲዮኖችን፣ የሚተላለፉና የማይተላለፉ የገንዘብ ሰነዶችንና ሌሎች ተመሳሳይ ተቀማጭ የገንዘብ ሀብቶችን መያዙን እና የተለያዩ ፈንዶችን ለታለመላቸው ዓላማ መዋላቸውን፤

13/  የፌደራል መንግስት ፋይናንስ እና ንብረት አስተዳደር በአግባቡ መከናወኑን እና ውጤታማ መሆኑን፤

14/  የአገሪቱን የኢኮኖሚ ዕድገት ቀጣይነት እና ፍትሃዊነት እንዲሁም የተረጋጋ የማክሮ - ኢኮኖሚ ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ፓሊሲዎች መመንጨታቸውን እና በአግባቡ ስራ ላይ መዋላቸውን ኢኮኖሚው በተገቢው መንገድ እየተመራ መሆኑን፤

15/  የአገሪቱ የልማት እቅድ እና የልማት ፕሮጀክቶች የአዘገጃጀትና አፈፃፀም ስርዓት መዘርጋቱን እንዲሁም በወቅቱ በስራ ላይ መዋሉን፤

16/  ለክልሎች የሚሰጥ ድጎማ በቀመሩ መሠረት መጽደቁን፤

17/  የአገሪቱ የስነ-ህዝብ ፓሊሲ መዘጋጀቱን፣ የማክሮ - ኢኮኖሚና የፊስካል ፖሊሲዎች መመንጨታቸውን እና በትክክል በስራ ላይ መዋላቸውን፤

18/  የኢኮኖሚ ትብብሮችና ትስስሮች ከመደረጋቸው በፊት በአገሪቱ የኢኮኖሚ አፈፃፀም ላይ የሚያስከትሉት ውጤት የሚፈተሽ እና የሚገመገም መሆኑን፤

19/  የፌደራል መንግሥት ዓመታዊ በጀት በአግባቡ ተዘጋጅቶ መቅረቡን እና መጽደቁን፤

20/  የአገሪቱ የገንዘብ እና የኢኮኖሚ ልማትና ትብብር ተግባራት በአግባቡ እየተከናወኑ መሆናቸውን፤

21/  ፌደራል መንግስት ታክስና ቀረጥ አስተዳደር እንዲሁም የመንግስት ገቢ አሰባሰብ በአግባቡ እየተከናወነ መሆኑን፤

22/  ትክክለኛ የሆነ የመንግስት የበጀት፣ የሂሳብ አያያዝ፣ የክፍያና የውስጥ ኦዲት ስርዓት መዘርጋቱንና በአግባቡ   እየተፈፀመ መሆኑን፤

23/  በመንግስት የኢኮኖሚና የፋይናንስ ፖሊሲ መሠረት የመንግስት የልማት ድርጅቶች በአገሪቱ የኢኮኖሚና ንግድ እንቅስቃሴ ገንቢ ሚና እያበረከቱ መሆኑን፤

24/  የፌዴራል አገር ውስጥ ገቢ አፈጻጸም ለማሻሻል እና ገቢ በአግባቡ እንዲሰበሰብ ለማድረግ ስትራቴጅዎችን መቅረፁን እና የአሰራር ስርአት መዘርጋቱን፤

25/  የፌዴራል አገር ውስጥ ገቢ የመሰብሰብ አቅም ግንባታን በቀጣይነት የሚያረጋግጡ አሠራሮችን መቀረፃቸውን እና አተገባበራቸውን፤

26/   ዘመናዊ የአገር ውስጥ ገቢ አወሳሰንና አሰባሰብ ሥርዓት መዘርጋቱንና ተግባራዊነቱን፤

27/  ታክስ ከፋዮች በፍቃደኝነት ታክስ የመክፈል ባሕልን እንዲያዳብሩ የሚያግዝ ስርዓት መዘርጋቱንና ተግባራዊ አፈፃፀሙን፤  

28/  ለክልል የገቢ ሰብሳቢ አካላት ተገቢውን የአቅም ግንባታ ድጋፍ መስጠቱን፣ የፌደራልና የክልል ታክስ አስተዳደር ሥርዓት የሚጣጣሙበትን ሁኔታ መፍጠሩን፤

29/  የመንግስት የልማት ድርጅቶች የስራ እንቅስቃሴ የገበያ ጉድለትን የሚሞላ እና የነፃ ገበያ ኢኮኖሚ ግንባታን የሚደግፍ እንዲሁም ትርፋማነትና የቴክኖሎጂ ሽግግርን የሚያረጋግጥ መሆኑን

30/  የሚከታተላቸውና የሚቆጣጠራቸው ተቋማትን የሚመለከቱ ፖሊሲዎች፣ ህጎች፣ ስትራቴጂዎች እና እቅዶች በአግባቡ በሥራ ላይ መዋላቸውን፤

31/  የሚከታተላቸውና የሚቆጣጠራቸው ተቋማት የተመደበላቸውን በጀት በአግባቡና በውጤታማነት በስራ ላይ ማዋላቸውን፡፡

የኮሚቴው ሰብሳቢዎች

የኮሚቴው ሪፖርት

የኮሚቴው አባላት