የሰው ኃይል እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች
የሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ተግባር እና ኃላፊነት
የሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሚከተሉት ጉዳዮች ላይ ክትትልና ቁጥጥር ያከናውናል፡-
1/ ፈጣን ልማት ለማምጣትና በዲሞክራሲ የታነፀ ሕብረተሰብን ለመፍጠር በብቃት፣ በጥራት፣ በታማኝነትና በቁርጠኝነት ሊሠራ የሚችል የሰለጠነ የህዝብ አገልጋይ የሰው ኃይል በአጭር ጊዜና በሰፊው ለማፍራት የሚደረገውን እንቅስቃሴ፤
2/ የትምህርትና ስልጠና ስታንዳርድ መውጣቱን፣ በየደረጃው ጥራትና አግባብነት ያለው ትምህርትና ስልጠና መሰጠቱንና የተማሪዎች ቅበላና ምደባ ፍትሃዊ መሆኑን፤
3/ የአጠቃላይና የከፍተኛ ትምህርት፣ ፖሊሲዎችን፣ ስትራቴጂዎች፣ ህጎችና እና ፕሮግራሞች መቀረፁን፤ አፈጻጸሙ ከሀገራዊ የልማት አቅጣጫ ጋር የተጣጣመ መሆኑን፤
4/ የአጠቃላይና የከፍተኛ ትምህርት የሥርዓተ-ትምህርት ማዕቀፍ መዘጋጀቱን፣ የትምህርት እና የትምህርት ተቋማትን ስታንዳርድ መውጣቱን፣ ሀገራዊ የብቃት ማዕቀፍ መዘጋጀቱን እና በሥራ ላይ መዋሉን፤
5/ የአጠቃላይና ከፍተኛ ትምህርት ፖሊሲና ሥርዓተ-ትምህርት መሠረት ያደረጉ ሀገር አቀፍ ፈተናዎች መዘጋጀታቸውን፣ እና የተማሪዎች ቅበላና ምደባ አፈጻጸም ፍትሃዊ መሆኑን፤
6/ ፐብሊክ ሰርቪሱ ብቃት ያለውና ውጤታማ መሆኑን፤ የፌዴራል መንግሥት ሠራተኞች ምልመላና መረጣ በብቃት ላይ የተመሰረተና ፐብሊክ ሰርቪሱ በቀጣይነት የሚለማበትና ጥቅም ላይ የሚውልበት እንዲሁም በብቃትና በአፈፃፀም ላይ የተመሰረተ የክፍያና የማበረታቻ ስርዓት መዘርጋቱንና ተግባራዊ መሆኑን፤
7/ የፌደራል መንግሥት ሠራተኞች የሥነ ምግባር መከታተያ ሥርዓት መዘርጋቱን፤ የመንግሥት ዘርፍ አገልግሎት አሰጣጥ ስታንዳርድና የቅሬታ አቀራረብና አፈታት ሥርዓት መዘርጋቱንና በቀጣይነት የሚሻሻልበት ስልት መቀየሱን፤
8/ የስራ፣ የስራ ስምሪትና ክህሎት፣ ፖሊሲዎች፣ ስትራቴጂዎችና ህጎችን መመንጨታቸውን፣ ለአፈጻጸሙ ከሀገራዊ የልማት አቅጣጫ ጋር የተጣጣመ ዝርዝር መርኃ ግብር መዘጋጀቱን እና ተግባራዊነቱንና ዉጤታማነቱን ፤
9/ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ከአገሪቱ አጠቃላይ የልማት ፖሊሲና ከሥራ ስምሪትና ክህሎት ዕድገት ጋር አብሮ ለማስኬድ የሚያስችል ስርአት መዘርጋቱን እና ውጤታማነቱን፤
10/ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ዘርፎች ጋር በመቀናጀት የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና የሥርዓተ-ሥልጠና ማዕቀፍ መቀረፁን እና የአተገባበሩን ውጤታማነት፤
11/ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ዘርፎች ጋር በማቀናጀት በቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ተቋማት እና በዘርፎቹ መካከል ለሥራ ገበያና ስምሪት እንቅስቃሴ የሚያግዝ ምቹ የእርስ በእርስ ትስስር ውጤታማነት፤
12/ የሰው ኃይል ልማትን ለማፋጠንና የቴክኖሎጂ አጠቃቀምና ውጤታማነት ለማሻሻል የሚረዱ የማሰልጠኛ ማዕከሎችን መቋቋማቸውን፣
13/ ከድህነት ወለል በታች ላሉት ላሉ ዜጎች የተለየ ፓኬጅ ተቀርጾ ወደ ሥራ መሠማራታቸውን፤
14/ የባዮ ቴክኖሎጂና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ፣ የጂኦ ስፓሻል፣ የስፔስ፣ የቴክኖሎጂ እና ዲጂታል ኢኮኖሚ ልማትንና ተወዳዳሪነትን በቀጣይነት የሚያረጋግጡ፣ ፖሊሲዎችን፣ ስትራቴጂዎች፣ ህጎችንና ፕሮግራሞች መቀረፃቸውን፣ ለአፈጻጸሙ ዝርዝር ከሀገራዊ የልማት አቅጣጫ ጋር የተጣጣመ መርኃ ግብር መዘጋጀቱን እና ተግባራዊ መደረጉን፤
15/ የሀገራዊ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ምርምርና ልማት ፖሊሲዎችን፣ ስትራተጂዎችን እና ፕሮግራሞችን አተገባበርና ውጤታማነትን፣
16/ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ልማት የግል ዘርፉን ተሳትፎና ሚና ለማሳደግ የሚያስችል ሥርዓት መዘርጋቱን አፈጻጸሙ ውጤታማ መሆኑን፣
17/ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አገልግሎቶች ጥራታቸው፣ ደህንነታቸውና አስተማማኝነታቸው የተጠበቀ እንዲሆን የሚያስችሉ ደረጃዎች መውጣታቸው እና ተግባራዊ መደረጋቸውን፤
18/ የቴክኖሎጂ ፍላጎት ለመዳሰስ፣ ተገቢ ቴክኖሎጂዎችን ለማፈላለግና በሥራ ላይ ለማዋል የሚያስችል ሥርዓት መዘርጋቱን፤
19/ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ በተለይ የዲጂታል መሰረተ ልማቶች ለማስፋፋት የሚያስችሉ ፕሮግራሞች በመቅረጽ ተግባራዊ መደረጉን፤
20/ የሚከታተላቸውና የሚቆጣጠራቸው ተቋማትን የሚመለከቱ ፖሊሲዎች፣ ህጎች፣ ስትራቴጂዎች እና እቅዶች በአግባቡ በሥራ ላይ መዋላቸውን፤
21/ የሚከታተላቸውና የሚቆጣጠራቸው ተቋማት የተመደበላቸውን በጀት በአግባቡና በውጤታማነት በስራ ላይ ማዋላቸውን፡፡