የውጭ ግንኙነት እና ሰላም ጉዳዮች

የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ተግባር እና ኃላፊነት

የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሚከተሉት ጉዳዮች ላይ ክትትልና ቁጥጥር ያከናውናል፡-

1/     የአገርና የሕዝብ ሰላም፣ ድህነትና ነፃነት እንዲከበሩ የሚያስችል ስልት የተነደፈ መሆኑና አስፈላጊው ግንዛቤና የንቅናቄ ስራ መከናወኑን፤

2/     በየትኛውም የአገሪቱ ክፍሎች የሚኖሩ ዜጎች መብትና ነፃነታቸው በተሟላ እንዲከበርና ጥበቃ እንዲያገኝ የፌደራሉ መንግስት ከክልል መንግስት ጋር በመተባበር እየሰራ መሆኑን፤

3/     በወሳኝ አገራዊ ጉዳዮች ብሔራዊ መግባባት ለመገንባት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን፤

4/     መንግስት የሚፈራረማቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች የአገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም የሚያረጋግጡና ሉዓላዊነትን የሚያስከብሩ፣ ከውጭ ግንኙነት መርሆና ፖሊሲ ጋር የተጣጣሙ መሆኑን፤

5/     መንግስት የሚያካሂዳቸው የውጭ ግንኙነት ተግባራት የአገሪቱን ዘላቂ ሰላም፣ ዲሞክራሲና ልማት የሚያረጋግጡ መሆኑን፤

6/     የውጭ ጉዳይ ፖሊሲና ስትራቴጂ እንዲሁም እቅዶችና ህጎች በአግባቡ በስራ ላይ መዋላቸውንና የሚፈለገውን ውጤት ማስገኘታቸውን፤

7/     የአገሪቷ የግዛት ሉዓላዊነት እየተከበረ መሆኑን፤

8/     የአገሪቱን ሉዓላዊነት ሊያስከብር የሚችል የብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦችን ተዋፆ የጠበቀ የመከላከያ ሰራዊት መደራጀቱን፤

9/     የአገር መከላከያ ሰራዊት አባላት የስራ ሁኔታና አስተዳደር በአግባቡ መጠበቁን፤

10/   ከሌሎች አገራት ጋር የሚደረጉ ወታደራዊ ስምምነቶችና አፈፃፀሞች፤

11/   ክፍለ አህጉራዊ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፍ የሰላም ስምምነቶችን፣ ግዴታዎችና አፈጻጸሞችን በተመለከተ፤

12/   የአገር መከላከያ ሰራዊት በሌሎች አገራት የሚያካሂዳቸውን የሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች፤

13/   ለሕገ-መንግሥቱና ለሕገመንግሥታዊ ስርዓቱ በታማኝነትና በፅናት የሚቆም፣ አገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተጨባጭ ሁኔታዎችን በማገናዘብ ዘመናዊና ጠንካራ ብሔራዊ የመረጃና ደህንነት አገልግሎት መገንባቱን፤ 

14/   ጥራት ያለው መረጃ በማቅረብና አስተማማኝ የደህንነት አገልግሎት በመስጠት የአገሪቷ ብሔራዊ ደህንነት እየተጠበቀ መሆኑን፤

15/   በግለሰቦችና በቡድኖች መካከል የሰላም፣ የመከባበርና የመቻቻል ባህል እንዲዳብር ለማድረግ የሚከናወኑ ተግባራትን፣

16/   የህዝብ ሠላም መጠበቁን እንደዚሁም አለመግባባቶችንና ግጭቶችን ለመከላከልና በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችል አሠራርና እንቅስቃሴ መኖሩን

17/   በፌደራል መንግስትና በክልሎች መካከል በመግባባትና በአጋርነት ላይ የተመሠረተ መልካም ግንኙነትና ትብብር እንዲጠናከር የሚደረገውን እንቅስቃሴ

18/   የአገሪቱን የመከላከያ እና የብሔራዊ መረጃና ደህንነት ፓሊሲዎችና ስትራቴጂዎች አፈፃፀምን፤

19/   የሚከታተላቸውና የሚቆጣጠራቸው ተቋማትን የሚመለከቱ ፖሊሲዎች፣ ህጎች፣ ስትራቴጂዎች እና ዕቅዶች በአግባቡ በሥራ ላይ መዋላቸውን፤

20/   የሚከታተላቸውና የሚቆጣጠራቸው ተቋማት የተመደበላቸውን በጀት በአግባቡና በውጤታማነት በስራ ላይ ማዋላቸውን፡፡

የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሌሎች ተግባራት

1/ ቋሚ ኮሚቴው ለምክር ቤቱ የሚቀርቡ ዓለም አቀፍ ስምምነቶች ከህገ-መንግስቱ እና ከአገሪቷ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ጋር የተጣጣሙ መሆናቸውን ይመረምራል፡፡

2/ ቋሚ ኮሚቴው ምክር ቤቱ ከሌሎች አገሮች ምክር ቤቶች እና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር የሚያካሂዳቸውን የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን የፓርላማ ዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን ያስተባብራል፣ አፈፃፀሙንም ይከታተላል፡፡

የኮሚቴው ሰብሳቢዎች

የኮሚቴው ሪፖርት

የኮሚቴው አባላት