የውጭ ግንኙነት እና ሰላም ጉዳዮች

የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ተግባር እና ኃላፊነት

የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሚከተሉት ጉዳዮች ላይ ክትትልና ቁጥጥር ያከናውናል፡-

1/     የአገርና የሕዝብ ሰላም፣ ድህነትና ነፃነት እንዲከበሩ የሚያስችል ስልት የተነደፈ መሆኑና አስፈላጊው ግንዛቤና የንቅናቄ ስራ መከናወኑን፤

2/     በየትኛውም የአገሪቱ ክፍሎች የሚኖሩ ዜጎች መብትና ነፃነታቸው በተሟላ እንዲከበርና ጥበቃ እንዲያገኝ የፌደራሉ መንግስት ከክልል መንግስት ጋር በመተባበር እየሰራ መሆኑን፤

3/     በወሳኝ አገራዊ ጉዳዮች ብሔራዊ መግባባት ለመገንባት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን፤

4/     መንግስት የሚፈራረማቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች የአገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም የሚያረጋግጡና ሉዓላዊነትን የሚያስከብሩ፣ ከውጭ ግንኙነት መርሆና ፖሊሲ ጋር የተጣጣሙ መሆኑን፤

5/     መንግስት የሚያካሂዳቸው የውጭ ግንኙነት ተግባራት የአገሪቱን ዘላቂ ሰላም፣ ዲሞክራሲና ልማት የሚያረጋግጡ መሆኑን፤

6/     የውጭ ጉዳይ ፖሊሲና ስትራቴጂ እንዲሁም እቅዶችና ህጎች በአግባቡ በስራ ላይ መዋላቸውንና የሚፈለገውን ውጤት ማስገኘታቸውን፤

7/     የአገሪቷ የግዛት ሉዓላዊነት እየተከበረ መሆኑን፤

8/     የአገሪቱን ሉዓላዊነት ሊያስከብር የሚችል የብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦችን ተዋፆ የጠበቀ የመከላከያ ሰራዊት መደራጀቱን፤

9/     የአገር መከላከያ ሰራዊት አባላት የስራ ሁኔታና አስተዳደር በአግባቡ መጠበቁን፤

10/   ከሌሎች አገራት ጋር የሚደረጉ ወታደራዊ ስምምነቶችና አፈፃፀሞች፤

11/   ክፍለ አህጉራዊ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፍ የሰላም ስምምነቶችን፣ ግዴታዎችና አፈጻጸሞችን በተመለከተ፤

12/   የአገር መከላከያ ሰራዊት በሌሎች አገራት የሚያካሂዳቸውን የሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች፤

13/   ለሕገ-መንግሥቱና ለሕገመንግሥታዊ ስርዓቱ በታማኝነትና በፅናት የሚቆም፣ አገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተጨባጭ ሁኔታዎችን በማገናዘብ ዘመናዊና ጠንካራ ብሔራዊ የመረጃና ደህንነት አገልግሎት መገንባቱን፤ 

14/   ጥራት ያለው መረጃ በማቅረብና አስተማማኝ የደህንነት አገልግሎት በመስጠት የአገሪቷ ብሔራዊ ደህንነት እየተጠበቀ መሆኑን፤

15/   በግለሰቦችና በቡድኖች መካከል የሰላም፣ የመከባበርና የመቻቻል ባህል እንዲዳብር ለማድረግ የሚከናወኑ ተግባራትን፣

16/   የህዝብ ሠላም መጠበቁን እንደዚሁም አለመግባባቶችንና ግጭቶችን ለመከላከልና በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችል አሠራርና እንቅስቃሴ መኖሩን

17/   በፌደራል መንግስትና በክልሎች መካከል በመግባባትና በአጋርነት ላይ የተመሠረተ መልካም ግንኙነትና ትብብር እንዲጠናከር የሚደረገውን እንቅስቃሴ

18/   የአገሪቱን የመከላከያ እና የብሔራዊ መረጃና ደህንነት ፓሊሲዎችና ስትራቴጂዎች አፈፃፀምን፤

19/   የሚከታተላቸውና የሚቆጣጠራቸው ተቋማትን የሚመለከቱ ፖሊሲዎች፣ ህጎች፣ ስትራቴጂዎች እና ዕቅዶች በአግባቡ በሥራ ላይ መዋላቸውን፤

20/   የሚከታተላቸውና የሚቆጣጠራቸው ተቋማት የተመደበላቸውን በጀት በአግባቡና በውጤታማነት በስራ ላይ ማዋላቸውን፡፡

የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሌሎች ተግባራት

1/ ቋሚ ኮሚቴው ለምክር ቤቱ የሚቀርቡ ዓለም አቀፍ ስምምነቶች ከህገ-መንግስቱ እና ከአገሪቷ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ጋር የተጣጣሙ መሆናቸውን ይመረምራል፡፡

2/ ቋሚ ኮሚቴው ምክር ቤቱ ከሌሎች አገሮች ምክር ቤቶች እና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር የሚያካሂዳቸውን የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን የፓርላማ ዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን ያስተባብራል፣ አፈፃፀሙንም ይከታተላል፡፡

የኮሚቴው ሰብሳቢዎች

የኮሚቴው ሪፖርት

የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን
የኢትዮጵያ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
የሰላም ሚኒስቴር
የኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስቴር

የኮሚቴው አባላት