ምክር ቤቱ የኢትዮዽያ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ረቂቅ አዋጅን አፀደቀ

 (ዜና ፓርላማ) ግንቦት 28 ቀን፣ 2017 .ም፤ የሕዝብ ተወካዮች /ቤት ዛሬ ባካሄደው 34 መደበኛ ስብሰባው የኢትዮዽያ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ረቂቅ አዋጅን አፅድቋል፡፡

የኢትዮዽያ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ የተከበሩ ፈቲህ ማህዲ (/) ለምክር ቤቱ ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ አቅርበዋል፡፡

የተከበሩ ፈቲህ (/) ባቀረቡት የውሳኔ ሀሳብ ረቂቅ አዋጁ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር መንግስት መር፣ በአገር በቀል አቅም የተገነባና ከተረጂነት  አስተሳሰብ በመሻገር ከጥገኝነትና ከጠባቂነት አስተሳሰብ የሚያላቅቅ ጠንካራ ሀሳብን የያዘ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

አያይዘውም አዋጁ ያልተማከለ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ስርዓትን የሚዘረጋና የፌደራልና የክልል መንግስታት በየደረጃው ተግባራቸውንና ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ የሚያስችል ድንጋጌዎችን የያዘ ነው ብለዋል፡፡

የአደጋ ሥጋት ቅበላ ተግባራቱ ከዘላቂ ልማት ዕቅዶችና ፕሮግራሞች ጋር የተሳሰሩና የሰብዓዊ ድጋፍ መርሆችን የተከተሉ እንዲሆኑ አሰራሮችን ያስቀመጠ፣ ከአደጋ በፊት፤ በአደጋ ጊዜና በድህረ አደጋ ወቅት ከቅድመ መከላከል እስከ መልሶ ማቋቋም ድረስ ያሉትን ውስብስብ ተግባራት ማከናወንና ውጤታማ ማድረግ የሚያስችል አደረጃጀት የሚፈጥር መሆኑንም ነው የገለጹት፡፡

የተከበሩ ፈቲህ (/) ረቂቅ አዋጁ ሲዘጋጅም የፌደራል ስርዓትን ከሚከተሉ ዘጠኝ አገራት ልምድና ተሞክሮ የተወሰደት በአይነቱ ልዩ የሆነ አዋጅ በመሆኑ ምክር ቤቱ ረቂቅ አዋጁን እንዲያፀድቀው ጠይቀዋል፡፡

የምክር ቤት አባላት በበኩላቸው ረቂቅ አዋጁ ሀገሪቱን ከረተጂነትና ከጠባቂነት አስተሳሰብ የሚያላቅቅና ሉዓላዊነቷን ማስጠበቅ የሚያስችል፣ እንዲሁም ነባር የሆነውን የመረዳዳት ባህል የሚያጠናክር መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በቀጣይ ከህብረተሰቡ የሚሰበሰቡ ገቢዎች ህግን፣ ደንብንና መመሪያዎችን መሰረት አድርገው መሆን እንዳለበትም የምክር ቤት አባላት አሳስበዋል፡፡

በመጨረሻም ምክር ቤቱ በረቂቅ አዋጁ ላይ በስፋት ከተወያየበት በኋላ የኢትዮዽያ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ረቂቅ አዋጅ ቁጥር 1386/2017 አድርጎ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል፡፡