ባለፉት 11 ወራት ከጠቅላላው የወጪ ንግድ 7.21 ቢሊዮን ዶላር ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚንስቴር አስታወቀ

 (ዜና ፓርላማ) ሰኔ 12 ቀን፣ 2017 .ም፤ በኢትዮጵያ ባለፉት 11 ወራት ከጠቅላላው የወጪ ንግድ 4.59 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ለማግኘት ታቅዶ 7.21 ቢሊዮን ማግኘት ስለመቻሉ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚንስቴር አስታውቋል፡፡ 

ዛሬ በተካሄደው 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4 ዓመት የስራ ዘመን 38 መደበኛ ስብሰባ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር 2017 በጀት ዓመት 11 ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ በምክር ቤቱ ውይይት ተደርጎበታል፡፡

የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሣሁን ጎፌ (/) ተቋሙ በበጀት ዓመቱ 11 ወራት ያከናወናቸውን ዋና ዋና ተግባራት በተመለከተ ለምክር ቤቱ አባላት ሪፖርትና ማብራሪያ አቅርበዋል፡፡

በበጀት ዓመቱ ባለፉት 11 ወራት ከግብርና ምርቶች፣ ከማኑፋክቸሪንግ፣ ከማዕድን፣ከኤሌክትሪክ እና ከሌሎች ዘርፎች ባአጠቃላይ 4.59 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ለማግኘት ታቅዶ 7.21 ቢሊዮን ዶላር (የዕቅዱን 157.26 በመቶ) ማሳካት ስለመቻሉ ገልጸዋል።

የተገኘው ገቢ ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር 3.96 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ወይም 121.48 በመቶ ብልጫ ስለማሳየቱም ሚኒስትሩ ጠቁመዋል፡፡

ለወጪ ንግድ ገቢ አፈጻጸም ዕድገት አስተዋፅኦ ካበረከቱት ጉዳዮች መካከል የገበያ መዳረሻዎችን ማስፋትና ነባሮቹን ማቆየት፣ በዓለም አቀፍ የንግድ ኤግዚቢሽኖች ላይ በመሳተፍ የወጪ ንግድ ምርቶቻችን ማስተዋወቅ ዋነኛው እንደሆነ ካሣሁን (/) አስረድተዋል፡፡

በበጀት ዓመቱ መጨረሻ ከወጪ ንግድ ገቢ አፈጻጸም 8 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ ገቢ እንደሚጠበቅ ነው ሚንስትሩ የተናገሩት፡፡

በሀገር አቀፍ ደረጃ ቀልጣፋ፣ ዘመናዊና ተደራሽ የንግድ አሰራርና የሸማቾች ጥበቃ ስርዓትን በመዘርጋትና በመቆጣጠር ባለፉት 11 ወራት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ተግባራት ማከናወናቸውንም ገልፀዋል፡፡

በበጀት ዓመቱ 11 ወራት የገበያ መሰረተ ልማትን በማስፋፋት አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ የሚያገናኙ የቅዳሜና እሁድ ግብይት ማዕከላትን ማስፋፋት፤ እንዲሁም የማህበረሰቡን የኑሮ ውድነት ጫና በመቀነስ የንግድ ስርዓቱን የተሳለጠ በማድረግ በገበያ ውስጥ በቂ የፍጆታ ምርቶች አቅርቦት ማረጋገጥ ስለመቻሉም አንስተዋል፡፡