የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የንብረት ማስመለስ ረቂቅ አዋጅ - Draft Laws
Participate
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የንብረት ማስመለስ ረቂቅ አዋጅ
Tigist T, modified 10 Months ago.
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የንብረት ማስመለስ ረቂቅ አዋጅ
Padawan Posts: 29 Join Date: 3/15/18 Recent Posts
የኢኮኖሚ ወንጀል በሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ በመሆኑ ይህንን ወንጀል መከላከል እና መቆጣጠር አስፈላጊ በመሆኑ እና ማንኛውም ሰው ከሕገ-ወጥ ድርጊት ማንኛውንም አይነት የኢኮኖሚ ጥቅም ማግኘት እንዳይችል የሚያደርግ ስርዓት በሕግ መዘርጋት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፥
በወንጀል የተገኘ ንብረትን ማጥናት፣ መለየት፣ ማገድ፣ መያዝ፣ መመርመር፣ መክሰስ፥ ንብረት ማስተዳዳር እና መውረስን የሚመለከቱ በተለያዩ ሕጎች ተበታትነው የሚገኙ ድንጋጌዎች በአንድ የሕግ ማዕቀፍ ውስጥ በማምጣት እና ለሁሉም የወንጀል አይነቶች እንዲያገለግሉ በማድረግ ለመሰረታዊ የሕግና የአፈጻጸም ጥያቄዎች ወጥነት ያለውና በቂ መልስ የሚሰጥ ሕግ ማውጣት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
ምንጩ ያልታወቀ ንብረት በሀገሪቱ የግብር ስርዓት፣ የውጭ ምንዛሬ፣ የገንዘብ ዝውውር ስርዓት እና የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ላይ ከፍተኛ አሉታዊ ተጽእኖ እያሳደረ በመሆኑእና ያለው የህግ ማዕቀፍ በመንግስት እና በህዝባዊ ድርጅት ሰራተኞች ላይ ብቻ የተወሰነ በመሆኑ ችግሩን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የሚያስችል የተሟላ የህግ ማዕቀፍ ማውጣት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ፤
ኢትዮጵያ በወንጀል የተገኘ ንብረት ማስመለስን በተመለከተ ያጸደቀቻቸውን ዓለም አቀፍ ስምምነቶች በተግባር ለማስፈጸም እና በወንጀል ድርጊት የሚገኝ ንብረትን ማስመለስ፤ መውረስና ማስተዳደርን በተመለከተ ዓለም አቀፍ መለኪያዎችን የሚያሟላ የሕግ ማዕቀፍ እንዲኖር ማድረግ በማስፈለጉ፤
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ህገ መንግስት አንቀፅ 55 (1) መሰረት የሚከተለው ታውጇል፡፡
በወንጀል የተገኘ ንብረትን ማጥናት፣ መለየት፣ ማገድ፣ መያዝ፣ መመርመር፣ መክሰስ፥ ንብረት ማስተዳዳር እና መውረስን የሚመለከቱ በተለያዩ ሕጎች ተበታትነው የሚገኙ ድንጋጌዎች በአንድ የሕግ ማዕቀፍ ውስጥ በማምጣት እና ለሁሉም የወንጀል አይነቶች እንዲያገለግሉ በማድረግ ለመሰረታዊ የሕግና የአፈጻጸም ጥያቄዎች ወጥነት ያለውና በቂ መልስ የሚሰጥ ሕግ ማውጣት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
ምንጩ ያልታወቀ ንብረት በሀገሪቱ የግብር ስርዓት፣ የውጭ ምንዛሬ፣ የገንዘብ ዝውውር ስርዓት እና የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ላይ ከፍተኛ አሉታዊ ተጽእኖ እያሳደረ በመሆኑእና ያለው የህግ ማዕቀፍ በመንግስት እና በህዝባዊ ድርጅት ሰራተኞች ላይ ብቻ የተወሰነ በመሆኑ ችግሩን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የሚያስችል የተሟላ የህግ ማዕቀፍ ማውጣት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ፤
ኢትዮጵያ በወንጀል የተገኘ ንብረት ማስመለስን በተመለከተ ያጸደቀቻቸውን ዓለም አቀፍ ስምምነቶች በተግባር ለማስፈጸም እና በወንጀል ድርጊት የሚገኝ ንብረትን ማስመለስ፤ መውረስና ማስተዳደርን በተመለከተ ዓለም አቀፍ መለኪያዎችን የሚያሟላ የሕግ ማዕቀፍ እንዲኖር ማድረግ በማስፈለጉ፤
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ህገ መንግስት አንቀፅ 55 (1) መሰረት የሚከተለው ታውጇል፡፡