null የኢትየጵያ ዲጂታል መታወቂያ አዋጅ

Tigist T, modified 1 Year ago.

የኢትየጵያ ዲጂታል መታወቂያ አዋጅ

Youngling Posts: 23 Join Date: 3/15/18
በኢትዮጵያ የዲጂታል መታወቂያ ሥርዓት መዘርጋት ነዋሪዎች የመታወቅ መብታቸው እንዲረጋገጥ፣ ሌሎች መብቶችን የመጠቀም እድሎችን ለማስፋት፣ የአገልግሎት ሰጪና ተቀባይ መካከል በሚኖር ግንኙነት ላይ እምነት እንዲዳብር፣ በአገር አቀፍ ደረጃ የግልጽነት ፣ የተጠያቂነት እና የተሳለጠ አሠራር ሥርዓትን ለመዘርጋት የሚያስችል በመሆኑ ፤
በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የበለፀገ፣ ዘርፍ ተሻጋሪ፣ መሠረታዊ የዲጂታል መታወቂያ ሥርዓት መዘርጋት ፤ ሃገራዊ ልማትን በአግባቡ ለማቀድ፣ ምጣኔ ሃብታዊ ሽግግር ለመፍጠር፣ መልካም አስተዳደርን ለማስፈን፣ የሀብት ብክነትን ለመቀነስ፣ ፖሊሲዎች ሲቀረጹ እና የልማት ሥራዎች ሲከናወኑ ድግግሞሽን ለመቅረፍ እና አካታችነትን ለማጎልበት የሚረዳ በመሆኑ፤