Participate

የሜዳይ፣ ኒሻን እና ሽልማት ረቂቅ አዋጅ አጭር ማብራርያ

ይህን አዋጅ ማዉጣት ያስፈለገበት ዓላማ፡- 1. በሀገሪቱ ብሎም በአፍሪካ ወይም ዓለም አቀፍ ደረጃ በተለያየ ዘርፎች ለሀገር እና ህዝብ እንዲሁም በአጠቃላይ ለሰዉ ልጆች የሚጠቅም የላቀ ተግባር የፈጸሙ ሰዎችን ወይም አካላትን እዉቅና በመስጠት ሌሎች የእነሱን አርአያነት እንዲከተሉ ማድረግ፤ 2. በህገ-መንግሰቱ መሰረት ማስፈጸሚያ አዋጅ ሳይወጣላቸዉ እየተሰጡ ያሉ የተለያዩ ሽልማቶችን ወጥ የሆነ ህጋዊ የአሰራር ስርዓት እንዲኖረዉ ለማስቻል ነዉ፡፡

Vote