የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ

President

የተከበሩ አቶ ታገሠ ጫፎ

መልዕክት

" በዴሞክራሲ ማሕበረሰብ ፓርላማ የፖለቲካ ተሳትፎ መገላጫ ነው፡፡ የፓርላማ ዴሞክራሲ ሥርዓት በአንድ አገር መጠናከር ለዜጎች የዴሞክራሲ ተሳትፎ መጎልበት፣ ለሕግ የበላይነትና ለማህበራዊ ፍትሕ መረጋገጥ ወሳኝ ሲሆን አስፈፃሚው የመንግሥት አካል በተጠያቂነትና በግልፅነት ስራውን እንዲያከናወን ያስችላል፡፡ በሀገራችን የፓርላማ ዴሞክራሲ ስርዓት መተግበር ከጀመረ ሦስት አስርት ዓመታት የተቆጠሩ ሲሆን አምስት የምክር ቤት ዘመናት አልፈው እነሆ አሁን በ6ኛው ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ላይ እንገኛለን፡፡ የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌደራሉ መንግሥት ከፍተኛ የሥልጣን አካል ነው፡፡ በየአምስት ዓመቱ በሚካሄድ ብሔራዊ ምርጫ የሕዝብ ይሁንታ አግኝተው በሚመረጡ አባላት ይመሰረታል፡፡ አባላቱም ሁሉ አቀፍ፣ ነፃ፣ ቀጥተኛ፣ ትክክለኛ በሆነና ድምጽ በሚስጥር በሚሰጥበት ሥርዓት በሕዝብ ይመረጣሉ፡፡አባላቱ ተጠሪነታቸው ለኢትዮጵያ ሕዝብ ነው፤ ተገዥነታቸውም ለሕገ መንግሥቱ፣ ለሕዝቡና ለሕሊናቸው ነው፡፡ ምክር ቤቱ በሕግ አወጣጥ፣ በክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም በውክልና ሥራዎች የሚያከናውናቸው ተግባራት እና የሚያስተላልፋቸው ውሳኔዎች ወሳኝ መሆናቸው ይታወቃል፤ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በእያንዳንዱ ዜጋ ሕይወት ላይ በአወንታዊም ሆነ በአሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደራቸው ግልፅ ነው፡፡
በጾታ
በፖለቲካ ፓርቲ

የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ሥልጣንና ተግባር:-

  • ሕግ ማውጣት፣
  • የፌደራል መንግስት በጀትን መርምሮ ማፅደቅ፣
  • መንግስታዊ አካላትን መከታተል፤ መቆጣጠር እና አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኝም እርምጃ መውሰድ፣
  • የራሱን የተለያዩ ኮሚቴዎችንና ሌሎች አስፈላጊ ክፍሎችን ማቋቋምና ማደራጀት፣
  • በራሱ የሚሰየሙ፣ የሚሾሙ እና የሚመረጡ የመንግስት ባለስልጣናትን መሰየም፣መሾም፣ማፅደቅና መምረጥ፣
  • አባላቱ ከመረጣቸው ህዝብ ጋር እንዲገናኙ  ማመቻቸት።

Image
📅

አዲስ መረሓ ግብር የለም

There are currently no scheduled events.

የጽ/ቤቱ ተልዕኮ፣ ረዕይ እና ዕሴቶች

ተልዕኮ

ጽ/ቤቱ የም/ቤቱ አባላትና አካላት ለሚያከናውኗቸው የሕግ አወጣጥ፣ ክትትልና ቁጥጥር፣ የውክልና እንዲሁም የፓርላማ ዲፕሎማሲ ተግባራት የማማከር፣ የጥናትና ምርምር አስተዳደራዊ አገልግሎት መስጠት እና የመረጃ ተደራሽነትን ማረጋገጥ ነው።

ርዕይ

በ2022 ነፃ፣ ገለልተኛና ጥራት ያለው ሙያዊና አስተዳዳራዊ አገልግሎት የሚሰጥ ጽ/ቤት መሆን፣

የተቋሙ ዕሴቶች

  • ለጋራ ስኬት መቆም፣
  • ቀጣይነት ያለው ለውጥ፣
  • ግልፅነትና ተጠያቂነት፣
  • መከባበርና መተባበር፣
  • ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት፣
  • ታማኝነትና ቅንነት፣
  • ውሳኔ ሰጭነት እና
  • ብዙኃነት ናቸው፡፡