ቋሚ ኮሚቴው የመንግስት ፕሮጀክቶች ክትትልና ቁጥጥር ስርዓት አፈፃፀም ላይ የተወሰደን የእርምት እርምጃ ሪፖርትን እያዳመጠ ይገኛል
---------------------
(ዜና ፓርላማ) መጋቢት 28፣ 2018 ዓ.ም፤ አዲስ አበባ ፤ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የመንግስት ፕሮጀክቶች ክትትልና ቁጥጥር ስርዓት አፈፃፀም ላይ በተሰራ የ2016/17 ክዋኔ ኦዲት ግኝት መሠረት በማድረግ የተወሰዱ የእርምት እርምጃ ሪፖርት እያዳመጠ ነው።
ቋሚ ኮሚቴው ታህሳስ 1 ቀን 2018 ዓ.ም የመንግስት ፕሮጀክቶች ክትትልና ቁጥጥር ስርዓት አፈፃፀም ላይ በተሰራ የ2016/17 ክዋኔ ኦዲት ላይ የፕላንና ልማት ሚኒስቴርን ጠርቶ ይፋዊ ውይይት ማድረጉ ይታወሳል።
በዚህ ይፋዊ ውይይት ቋሚ ኮሚቴው ካስቀመጣቸው አቅጣጫዎች መካከል የፕላንና ልማት ሚኒስቴር፣ ከገንዘብ ሚኒስቴርና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ጋር የጋራ ውይይት አድርጎ የፕሮጀክቶቹ ግልጽ አመራር ማድረግ መሆኑ የሚታወስ ነው።
ይህ ውይይትም የክዋኔ ኦዲት ግኝቱን መሠረት በማድረግ የተወሰዱ የእርምት እርምጃዎችን ሪፖርት ለመገምገም የተዘጋጀ መድረክ መሆኑን የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ የሺመቤት ደምሴ (ዶ/ር) ገልፀዋል።
የእርምት እርምጃ ሪፖርቱን የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ፍፁም አሰፋ እና ሌሎች የስራ ኃላፊዎች እያቀረቡ ይገኛሉ።
(በ አለማየሁ ጌቴ)






ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament
በዩቲዩብ
https://www.youtube.com/@FDREHOPR
በቴሌግራም
በትዊተር
በዌብሳይት
www.hopr.gov.et ይከታተሉ።