"ዩኒቨርሲቲው ውስጣዊ አቅሙን በማጠናከር ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ ይጠበቅበታል" --- ቋሚ ኮሚቴው

--------------------

(ዜና ፓርላማ) መጋቢት 18 2018 .ም፣ ነቀምቴ፣ ወለጋ ዩኒቨርሲቲ ተቋማዊ ተልዕኮውን ከግብ ለማድረስ ውስጣዊ አቅሙን በማጠናከር ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚጠበቅበት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ኃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስገንዝቧል፡፡

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ ነገሪ ሌንጮ (/) ዩኒቨርሲቲው ተልዕኮን መሰረት በማድረግ የትምህርት ፕሮግራሞችን፣ ምርምርና ስልጠና የልህቀት ማዕከላትን ማስፋፋት ይጠበቅበታል ብለዋል።

አክለውም ውስጣዊ አቅሙን በማስተባበርና በማቀናጀት ሀገርን የሚለውጡ ተጨባጭ ተግባራትን ማከናወን ይጠበቅበታል ብለዋል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ተኮር የጥናትና ምርምር ሥራዎችን በማከናወን፣ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በማስተዋወቅ፣ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ በሚያደርጉ ተግባራት ላይ በመሳተፍ ትልቅ ተሞክሮ እንዳለው ገልፀው፣ ይህንኑ ማስቀጠል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የዩኒቨርሲቲው አመራር ለለውጥ ያለውን ፍላጎት እና ቁርጠኝነት በተግባር ማሳየቱን ጠቁመው፣ በቀጣይ ተቋሙ ከዚህ በተሻለ ሁኔታ እንዲገኝ የሚያስችል እንቅስቃሴ ማድረግ ይገባልም ብለዋል፡፡

የቋሚ ኮሚቴው አባል የተከበሩ መብራቱ አለሙ (/) በበኩላቸው የተቋሙ አመራር ለለውጥ ያለው ዝግጁነት ከችግር ለመውጣት ድጋፍ ከሚያደርጉለት አካላት ጋር አብሮ ለመሥራት ያለው ቁርጠኝነት እና ለአካባቢው ህብረተሰብ የሚሰጠው የማኅበረሰብ አገልግሎት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።

የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ፣ የመምህራንን አቅም ለማሳደግ የተከናወኑ ሥራዎች፣ ተግባር ተኮር የጥናትና ምርምር የማኅበረሰብ አገልግሎት ሥራዎች፣ በየጊዜው የሚከሰቱ ችግሮችን በፍጥነት ለመፍታት የሚያስችል ቅንጅታዊ አሠራር መዘርጋቱ፣ ከፈጠራና ከቴክኖሎጂ ሽግግር አንፃር የተሰሩ ሥራዎች በቋሚ ኮሚቴው በጥንካሬ ተነስተዋል፡፡

የዩኒቨርሲቲው ቦርድ አመራሩና መምህራን ተቀናጅተው አለመስራታቸው የኢንዱስትሪ እና ዩኒቨርሲቲ ትስስር አለመጠናከር በቀጣይ ሊሻሻሉ እንደሚገባ የቋሚ ኮሚቴው አባላት አመላክተዋል፡፡

የወለጋ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ተስፋዬ ለማ (/) ዩኒቨርሲቲው የአካባቢውን ፀጋ በመለየት በግብርናው፣ በማዕድን ዘርፍ የልህቀት ማዕከል ለመሆን የተሰጠውን ተልዕኮ በውጤታማነት ተግባራዊ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡

አክለውም ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት አንዲፈጠር ከባለድርሻ አካላት ጋር በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የመምህራን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመፍታት ከከተማው አስተዳደር ጋር በመነጋገር የመሬት አቅርቦት እንዲኖር ጥረት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

የወለጋ ዩኒቨርስቲ አካዳሚክ ምክትል ፕሬዚዳንት መልካ ኢካ (/) በበኩላቸው ተማሪዎች መውጫ ፈተና በተሻለ ውጤት እንዲያልፉ ዩኒቨርስቲው አስፈላጊውን ድጋፍ እያከናወነ መሆኑን አስረድተዋል።

(- ኃይለማርያም አየለ)

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament

በዩቲዩብ

https://www.youtube.com/@FDREHOPR

በቴሌግራም

https://t.me/ParlamaNews

በትዊተር

http://twitter.com/fdrehopr

በዌብሳይት

www.hopr.gov.et ይከታተሉ።