የንግድ ስርዓቱን ቀልጣፋ፣ ዘመናዊና ተደራሽ ለማድረግ እየተሰሩ ያሉ ሥራዎችን ማጠናከር እንደሚገባ ቋሚ ኮሚቴው አመለከተ

-------------------

(ዜና ፓርላማ) መጋቢት 23 2018 .ም፤ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር የንግድ ስርዓቱን ቀልጣፋ፣ ዘመናዊና ተደራሽ ለማድረግ እየተሰሩ ያሉ ሥራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንዳለበት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ

አሰገንዝቧል፡፡

ቋሚ ኮሚቴው የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴርን 2018 በጀት ዓመት የስምንት ወራት የስራ ክንውን ሪፖርት ገምግሟል፡፡

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ / አሻ ያህያ የንግድን ስርዓቱን ቀልጣፋ፣ ዘመናዊና ተደራሽ ለማድረግ የተሰሩት የኦንላይን ፈቃድ አሰጣጥ፣ የንግድ ፈቃድ ለማውጣት የሚያስፈልገውን ረጅም ሂደት አሰራር በመዘርጋት መሻሻሉ ትልቅ እምርታ የታየበት በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አመላክተዋል።

የዋጋ ንረትን ለማረጋጋት እና አምራችና ሸማቹን በቀጥታ ለማገናኘት የእሁድና ቅዳሜ ገበያ ማዕከላትን በማስፋት የተወሰዱ እርምጃዎች የሚበረታቱ ተግባራት መሆናቸውን ሰብሳቢዋ ገልጸው፤ ገበያን ለማረጋጋት ትልቅ ሚና ይጫወታሉም ብለዋል።

በተያያዘም ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡና እንዲሁም ከሀገር የሚወጡ ምርቶች ላይ እየተደረገ ያለው ጠንካራ ቁጥጥር የሚበረታታ መሆኑን ተናግረዋል።

የተከበሩ / አሻ ያህያ አያይዘውም፤ መሰረታዊ የፍጆታ እቃዎች ላይ የተለያዩ ድጎማዎችን በሚመለከት ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን የማህበረሰብ ክፍሎች ላይ ትኩረት ማድረግ እንዲሁም በሀገር ውስጥ የሚመረቱ ምርቶች ጥራት ላይ ያለው ቁጥጥር አጠናክሮ መቀጠል ያስፈልጋልም ሲሉ አሳስበዋል።

ከነዳጅ ጋር በተያያዘ በወቅቱ ያለውን ዓለማቀፍ ቀውስ እንዳለ ሆኖ ነዳጅን ተደራሽ ከማድረግ አኳያ ብዙ መልስ የሚያስፈልጋቸው ቦታዎች በመኖራቸው ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

የንግድ ዘርፍ ማህበራት ሚናቸው የጎላ በመሆኑ የንግዱን ዘርፍ ከማሳደግ እንዲሁም ህገ-ወጥነት ከመከላከል አንፃር ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የቅርብ ክትትል ማድረግ እንዳለበት የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ ዮሐንስ መስፍን አስገንዝበዋል።

የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (/) የነዳጅን ተደራሽነት ለማስፋፋት በዘርፋ ያለውን ከፍተኛ ህገ-ወጥ ተግባር በመቆጣጠር ከፍተኛ አፈፃፀም ለማስመዝገብ ከቋሚ ኮሚቴው ጋር በትብብር እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

አክለውም ሚኒስትሩ በቋሚ ኮሚቴው በጥንካሬ የተነሱትን ለማስቀጠል እንዲሁም ትኩረት የሚያስፈልጋቸውን ጉዳዮች ለማሻሻል እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

(- ቃልኪዳን ተሰማ)

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament

በዩቲዩብ

https://www.youtube.com/@FDREHOPR

በቴሌግራም

https://t.me/ParlamaNews

በትዊተር

http://twitter.com/fdrehopr

በዌብሳይት

www.hopr.gov.et ይከታተሉ።