አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ራስ ገዝ ለመሆን የሚያስችል ዝግጅት እያከናወነ መሆኑ ተገለፀ

--------------------

(ዜና ፓርላማ) መጋቢት 18 2018 .ም፣ አርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ራስ ገዝ ለመሆን የሚያስችል ዝግጅት እያከናወነ መሆኑ ተገልጿል።

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ኃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ የምርምር ዩኒቨርሲቲ ልየታ መሰረት በተሰጠው ተልዕኮ የመማር ማስተማር፣ የጥናትና ምርምር እንዲሁም የማህበረሰብ ጉድኝት ተልዕኮ ያለበትን ደረጃ ለመከታተል ያግዘው ዘንድ ከዩኒቨርሲቲው የስራ ኃላፊዎች ጋር የመግቢያ ውይይት አካሂዷል።

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ ነገሪ ሌንጮ (/) ዩኒቨርሲቲው በሀገራችን ከሚገኙ የመጀመሪያው ትውልድ ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ መሆኑን ጠቁመው፣ ዩኒቨርሲቲው ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቀጥሎ ወደ ፊት ራስ ገዝ ይሆናሉ ተብለው ከሚጠበቁ አንጋፋ እና የልህቀት ተቋማት አንዱ መሆኑን ተናግረዋል።

ቋሚ ኮሚቴው በመስክ ጉብኝቱ ከሪፖርት ባሻገር መሬት ላይ የተከናወኑ ስራዎች ላይ የመስክ ምልከታ የሚያከናውን መሆኑን ተጠቁሟል።

የአርባ ምንጭ በዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ኢንጅነር አብደላ ከማል (/) 2018 በጀት ዓመቱን የስድስት ወራት የስራ ክንውን ሪፖርትን በዝረዝር አቅርበዋል፡፡

ኢንጅነር አብደላ ከማል (/) ዩኒቨርሲቲው ወደ ራስ ገዝነት ለመሸጋገር የሚያስችለውን በዳይሬክተር የሚመራ ልዮ ቢሮ በማቋቋም፤ 10 ዓመት ፍኖተ ካርታ በመቀርፅ 28 የሚደርሱ መመሪያዎችና ፖሊሲዎችን ማዘጋጀቱን አንስተው፤ ዩኒቨርሲቲው ራስ ገዝ ለመሆን 96 በመቶው ዝግጅት መደረጉን አስረድተዋል፡፡

ዩኒቨርሲቲው በትኩረት መስክ ልየታ በውሃ መስክ መሪ በኢንጅነሪንግ፣ ግብርና፣ ጤና ሳይንስ እንዲሁም በማህበራዊ ሳይንስ ልህቀት ማዕከል የመሆን ራዕይ አንግቦ በልየታ መሰረት የተሰጡ አጀንዳዎችን በተጠናከረ መልኩ እያከናወነ እንደሚገኝ አያይዘው አስረድተዋል፡፡

በሰላማዊ መማር ማስተማር፣ በችግር ፈቺ ጥናትና ምርምር፣ እንዲሁም በቴክኖሎጂ ሽግግርና ስርጸት ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን በውጤታማነት ማከናወን መቻሉንም ፕሬዝዳንቱ ገልጸዋል፡፡

(-ኃይለማርያም አየለ)

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament

በዩቲዩብ

https://www.youtube.com/@FDREHOPR

በቴሌግራም

https://t.me/ParlamaNews

በትዊተር

http://twitter.com/fdrehopr

በዌብሳይት

www.hopr.gov.et ይከታተሉ።