የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ

President

የተከበሩ አቶ ታገሠ ጫፎ

መልዕክት

"

በዴሞክራሲ ማሕበረሰብ ፓርላማ የፖለቲካ ተሳትፎ መገላጫ ነው፡፡ የፓርላማ ዴሞክራሲ ሥርዓት በአንድ አገር መጠናከር ለዜጎች የዴሞክራሲ ተሳትፎ መጎልበት፣ ለሕግ የበላይነትና ለማህበራዊ ፍትሕ መረጋገጥ ወሳኝ ሲሆን አስፈፃሚው የመንግሥት አካል በተጠያቂነትና በግልፅነት ስራውን እንዲያከናወን ያስችላል፡፡ በሀገራችን የፓርላማ ዴሞክራሲ ስርዓት መተግበር ከጀመረ ሦስት አስርት ዓመታት የተቆጠሩ ሲሆን አምስት የምክር ቤት ዘመናት አልፈው እነሆ አሁን በ6ኛው ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ላይ እንገኛለን፡፡ የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌደራሉ መንግሥት ከፍተኛ የሥልጣን አካል ነው፡፡ በየአምስት ዓመቱ በሚካሄድ ብሔራዊ ምርጫ የሕዝብ ይሁንታ አግኝተው በሚመረጡ አባላት ይመሰረታል፡፡ አባላቱም ሁሉ አቀፍ፣ ነፃ፣ ቀጥተኛ፣ ትክክለኛ በሆነና ድምጽ በሚስጥር በሚሰጥበት ሥርዓት በሕዝብ ይመረጣሉ፡፡አባላቱ ተጠሪነታቸው ለኢትዮጵያ ሕዝብ ነው፤ ተገዥነታቸውም ለሕገ መንግሥቱ፣ ለሕዝቡና ለሕሊናቸው ነው፡፡ ምክር ቤቱ በሕግ አወጣጥ፣ በክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም በውክልና ሥራዎች የሚያከናውናቸው ተግባራት እና የሚያስተላልፋቸው ውሳኔዎች ወሳኝ መሆናቸው ይታወቃል፤ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በእያንዳንዱ ዜጋ ሕይወት ላይ በአወንታዊም ሆነ በአሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደራቸው ግልፅ ነው፡፡ በመሆኑም ምክር ቤቱ ለሀገር ሠላም፣ ለዜጎች ማህበራዊ ልማትና ሁለንተናዊ ብልፅግና መረጋገጥ አስፈላጊ ናቸው ተብለው በታመኑ ጉዳዮች ላይ በሕግ አወጣጥ ሂደት፣ በክትትልና ቁጥጥር እና በውክልና ተግባራት ተገቢውን ምርመራ በማካሂድ በርካታ ሀገራዊ ውሳኔዎችን ሲያሳልፍ ቆይቷል፡፡ ለሀገራዊ እቅዶች፣ፕሮግራሞች፣ፖሊሲዎችና ፕሮጀክቶች መፈፀም ፤ የመንግሥትና ሕዝብ ሃብትና ንብረት ለታለመለት ዓላማ ውለው የሕዝብ የኑሮ ደረጃ እንዲሻሻል የመንግሥት ተቋማት ተልዕኳቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ምክር ቤቱ ጠንከራ የክትትልና ቁጥጥር ስራ ሰርቷል፤ እየሰራም ይገኛል፡፡ ህብረተሰቡ የሚያነሳቸው የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ ምክር ቤቱ ከመቼውም ጊዜ በላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ሲሆን የተቋማት ምላሽም እያደገና እየተሻሻለ መጥቷል ማለት ይቻላል፡፡ በፓርላማ ዲፕሎማሲው ዘርፍ የሀገራችንን ባሕልና እውነተኛ ገፅታ ለማስተዋወቅና የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ (ንግድና ኢንቨስትመንት) ከመደገፍ ረገድ አበረታች ውጤቶች ለማስመዝገብ የሁለትዮሽና በብዙኽዮሽ መድረኮችን በአግባቡ ለመጠቀም ጥረት ተደርጓል፤ በቀጣይም የፓርላማ ዲፕሎማሲን እንደ አንድ የውጭ ፖሊሲ መሳሪያ በስፋትና በተጠናከረ አግባብ ተግባራዊ ለማድረግ ምክር ቤቱ በትኩረት የሚሰራ ይሆናል፡፡ የዜጎችን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል የተጓተቱ ፕሮጀክቶች ፈጥነው ተጠናቀው ለህብረተሰቡ የልማት አገልግሎት እንዲሰጡ፣ኢንቨስትመንት እንዲስፋፋ፣በሥራ ፈጠራና ድህነት ቅነሳ፣ ለሕግ የበላይነትና ለመልካም አስተዳደር መረጋገጥ ምክር ቤቱ በቀጣይ ጊዜያት በትኩረት የሚሰራ ይሆናል፡፡ ያሉብንን የፖለቲካ ልዩነቶች በንግግር፣ በምክክርና በውይይት ለመፍታት ምክር ቤቱ የአቋቋመው ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በአሁኑ ወቅት በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ ይገኛል፡፡ ለኮሚሽኑ ተልዕኮ መሳካት ሁላችንም ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን በሀገራዊ የፍቅር ስሜት የበኩላችን ድርሻ ልንወጣ ይገባል፡፡ የአንድነታችን ተምሳሌትና የአብሮነታችን ማሳያ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድባችን በመጠናቀቅ ሂደት ላይ የሚገኝ ሲሆን የዜጎችን ማህበራዊ ኢኮኖሚ ልማት የሚያፋጥኑ በርካታ ትላልቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ ሥለሆነም ሀገራችን የጀመረችውን ሁለንተናዊ ብልፅግና ጉዞ ከዳር ለማድረስና ለዜጎቿ ምቹ የሆነች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ለሠላም፣ ለአብሮነታችን መጎልበትና ለብሔራዊ መግባባት አብረን እንድንቆምና ሁላችንም የየራሳችንን አበርክቶ እንድንወጣ በዚህ አጋጣሚ መልዕክት አስተላልፋለሁ፡፡ አዲሱ ዓመት የሠላም፣ የደስታ፣ የአብሮነት፣ የመግባባት፣ የልማት እና ብዙ ተስፋዎች የምናይበት ዘመን እንዲሆን ልባዊ ምኞቴ ነው፡፡ አመሠግናለሁ!

የፌዴራል የስፖርት ልማት እና አስተዳደር አዋጅ በሙሉ ድምፅ ጸደቀ

የፌዴራል የስፖርት ልማት እና አስተዳደር አዋጅ በሙሉ ድምፅ ጸደቀ

*********************

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 15 መደበኛ ስብሰባ፣ የስፖርት ዘርፍ ላይ መሠረታዊ ለውጥ ያመጣል ተብሎ የታመነበትን የፌዴራል የስፖርት ልማት እና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ መርምሮ አጽድቋል።

አዲሱ አዋጅ ቁጥር 1413/2018 በስፖርቱ ዘርፍ አካታች፣ ዘመናዊና ግልጽነት ያለው የአሰራር ሥርዓት ለመዘርጋት ምቹ መደላድል የሚፈጥር ሲሆን፣ በዘርፉ የሚታዩ የአሰራርና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ታላቅ ፋይዳ እንዳለው ተገልጿል።

አዋጁ የስፖርት መሠረተ ልማቶችንና ማሰልጠኛ ተቋማትን ከማስፋፋት ባለፈ፣ የስፖርት ግብዓት አምራቾች እንዲበረታቱና ዘርፉ ለሀገር ኢኮኖሚ የራሱን ድርሻ እንዲያበረክት ያደርጋል።

በተጨማሪም ማህበራዊ ትስስርን በማጎልበት፣ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን በማጠናከር እና ስፖርት ነክ ወንጀሎችን በመከላከል ረገድ ጉልህ ሚና እንደሚጫወት በምክር ቤቱ የጤና፣ ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወርቀሰሙ ማሞ አብራርተዋል።

የባህልና ስፖርት ሚኒስትር / ሸዊት ሻንካ በሰጡት ማብራሪያ፣ ስፖርት የኢትዮጵያውያን የኩራት ምንጭ እንዲሆን ዘርፉን የያዙ ማነቆዎችን በአሰራርና በስርዓት መፍታት የግድ እንደሚል ጠቁመዋል።

አዋጁ ከዘርፉ ማግኘት ያለባትን ጥቅም እንድታገኝ በማድረግ ረገድ መሠረታዊ ለውጥ እንደሚያመጣ ሚኒስትሯ ገልጸዋል።

የምክር ቤቱ አባላትም የአዋጁን አስፈላጊነት በማመንና አፈጻጸሙ ላይ ትኩረት እንዲደረግ በማሳሰብ አዋጁን በሙሉ ድምፅ ማጽደቁን ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

 

የሴኩዩሪቲ አገልግሎት ክፍያ አካትቶ የተሻሻለው የኢትዮጵያ አቭየሽን ሴኩሪቲ አዋጅ ፀደቀ።

ሚያዝያ 13/ 2018

የሴኩዩሪቲ አገልግሎት ክፍያ አካትቶ የተሻሻለው የኢትዮጵያ አቭየሽን ሴኩሪቲ አዋጅ ፀደቀ።

የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለሚሰጠው የአቭየሽን አገልግሎት ከተገልጋዮች ክፍያ መስብሰብ የሚያስችለውን አዋጅ በአብላጫ ድምፅ አፅድቋል።

በአየር ትራንስፖርት ስርዓቱ የሚቃጡ የሕገ ወጥ ጣልቃ ገብ ድርጊቶች፣ ባህሪያትና የአፈፃፀም ስልት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገና እየተወሳሰበ በመምጣቱ፤ ነባሩ አዋጅ ከሃያ ዓመታት በላይ ሳይሻሻል የቆየ በመሆኑ፤ ዘመን ያመጣቸውን ውስብስብ ህገ ወጥ ጣልቃ ገብ ድርጊቶችን ለመቆጣጠር የሚያስችል እንዲሁም ወቅቱን የዋጀ የህግ ማዕቀፍ መደንገግ የሚያስፈልግ በመሆኑ አዋጁን ማሻሻል እንዳስፈለገ ተነግሯል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የዓለም አቀፍ ሲቪል አቭዬሽን ድርጅት ከራሱ መንገደኞች፣ ከሌሎች ኦፕሬተሮች እና በኤርፖርት ውስጥ የአቪዬሽን ሴኪዩሪቲ አገልግሎት ከሚያገኙ ማናቸውም አካላት የአገልግሎት ክፍያ በመሰብሰብ ለብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ገቢ እንዲያደርግ በአዋጁ ተደንግጓል።

ከአገልግሎት ክፍያ የሚሰበሰበው ገቢ ለኤርፖርት የሴኩዩሪቲ ቴክኖሎጂ ግዢ፣ ለአቭዬሽን ሴኩዩሪቲ የፀጥታ አካላት ሥልጠናና አቅም ግንባታ፣ ለአነፍናፊ ውሻ ግዥና ሥልጠና፣ ለጥገናና ማስፋፊያ እንዲሁም አሠራርን ለማዘመን የሚውል መሆኑም በአዋጁ ተካትቷል።

ምንታምር ፀጋው

 

ምክር ቤቱ የባለብዙ ተዋንያን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅን መርምሮ አፀደቀ

ምክር ቤቱ የባለብዙ ተዋንያን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅን መርምሮ አፀደቀ

----------------------

(ዜና ፓርላማ) መጋቢት 29 2018 .ም፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 14 መደበኛ ስብሰባው የባለብዙ ተዋንያን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅን መርምሮ አጽድቋል፡፡

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ ሰለሞን ላሌ ሪፖርት እና የውሳኔ ሀሳብ አቅርበዋል፡፡

ረቂቅ አዋጁ በመንግስት ብቻ የሚሰጠው የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎት በቂ ባለመሆኑ ወቅቱ የሚጠይቀውን የባለብዙ ተዋንያን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎት ሥርዓት እንዲዘረጋ ምቹ መደላድል እንደሚፈጥር ሰብሳቢው አመላክተዋል፡፡

በዲጂታል ግብርና ኤክስቴንሽን የሚያማክሩ እና የመረጃ ቅብብሎሽ አገልግሎት የሚሰጡ የግል ባለሀብቶች ፣መንግስታዊ ያልሆኑ እና የሆኑ ድርጅቶች እየታዩ በመሆኑ በግብርና ኤክስቴንሽን ውስጥ አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስችል ረቂቅ አዋጅ መሆኑን የተከበሩ አቶ ሰለሞን ላሌ አያይዘው አስገንዝበዋል፡፡

የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎት አሰጣጡ ጥራትና ፍትሃዊነት ቁጥጥር ትኩረት የሚሻ በመሆኑ አገልግሎት የሚሰጠው በተመዘገበና የብቃት ማረጋገጫ ባገኘ አገልግሎት አቅራቢ መሆን እንደሚኖርበት አዋጁ የአሰራር ሥርዓት እንዳስቀመጠ ጠቁመዋል፡፡

የግብርና ኤክስቴንሽን መሰረት ልማት ዝርጋታዎችን ማዘመን በመንግስት ላይ ብቻ በመውደቁ በሚጠበቀው ደረጃ እርካታ ያልተገኘበትን የተጠቃሚዎች ፍላጎት ምላሽ ለመስጠት የግብርና ኤክስቴንሽን ፈንድ ለማቋቋምና ፍላጎት ለመቅረፍ ረቂቅ አዋጁ እንዳካተተ ሰብሳቢው አንስተዋል፡፡

በግብርና ባለሙያዎች ብቻ ይሰጥ የነበረው የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎት አሁን ላይ የምርት መጠንና ምርታማነትን ለማሳደግ በቂ ምላሽ ባለመስጠቱ ይህንን ችግር ለመፍታት አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎቱን ለማሻሻልና ለማዘመን ረቂቅ አዋጁ አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡

የሀገራችን ኢኮኖሚ በግብርና ላይ የተመሰረተ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ሰለሞን ላሌ፣ በዘርፉ ምርትን በብዛት፣ በጥራትና በቀጣይነት ለማሳደግ የግብርና ኤክስቴንሽን ከፍተኛ ሚና እንዳለው ገልጸዋል፡፡

የምክር ቤት አባላት በበኩላቸው፣ ከግብርና ምርምር የሚገኙና ከውጭ የሚመጡ ቴክኖሎጂዎችን የግብርና ባለሙያው ለአርሶ አደሮች በተግባር ማሳ ላይ እያሳዩና እያስተማሩ አገልግሎት መስጠት እንዳለባቸው አስተያየት ሰጥተዋል፡፡

የምክር ቤት አባላቱ አያይዘውም የግብርና ኤክስቴንሽን ተደራሽነት 36% በላይ አለማለፉን ጠቁመው፣ ረቂቅ አዋጁ ይህንን ክፍተት እንደሚሞላ ገልጸዋል፡፡

ረቂቅ አዋጁ መንግስታዊ ያልሆኑ የአገልግሎት ተዋንያን ህጋዊነትን በጠበቀ መልኩ፣ ተጠያቂነት በሰፈነበት እና ጥራቱ በጠበቀ ሁኔታ መንግስትን እና አርሶ አደሩን በመደገፍ የግብርና ልማቱን በሚገባ እንደሚያሳልጥ ጠቁመዋል።

በመጨረሻም ምክር ቤቱ በረቂቅ አዋጁ ላይ ሰፊ ውይይት ካደረገ በኋላ፣ የባለብዙ ተዋንያን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅን፣ አዋጅ ቁጥር 1411/2018 ሆኖ በሙሉ ድምጽ አጽድቆታል፡፡

( አገሪቱ ጌቴ)

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament

በዩቲዩብ

https://www.youtube.com/@FDREHOPR

በቴሌግራም

https://t.me/ParlamaNews

በትዊተር

http://twitter.com/fdrehopr

በዌብሳይት

www.hopr.gov.et ይከታተሉ።

 

ቋሚ ኮሚቴው የመንግስት ፕሮጀክቶች ክትትልና ቁጥጥር ስርዓት አፈፃፀም ላይ የተወሰደን የእርምት እርምጃ ሪፖርትን እያዳመጠ ይገኛል

ቋሚ ኮሚቴው የመንግስት ፕሮጀክቶች ክትትልና ቁጥጥር ስርዓት አፈፃፀም ላይ የተወሰደን የእርምት እርምጃ ሪፖርትን እያዳመጠ ይገኛል

‎---------------------

‎(ዜና ፓርላማ) መጋቢት 28 2018 .ም፤ አዲስ አበባ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የመንግስት ፕሮጀክቶች ክትትልና ቁጥጥር ስርዓት አፈፃፀም ላይ በተሰራ 2016/17 ክዋኔ ኦዲት ግኝት መሠረት በማድረግ የተወሰዱ የእርምት እርምጃ ሪፖርት እያዳመጠ ነው።

ቋሚ ኮሚቴው ታህሳስ 1 ቀን 2018 . የመንግስት ፕሮጀክቶች ክትትልና ቁጥጥር ስርዓት አፈፃፀም ላይ በተሰራ 2016/17 ክዋኔ ኦዲት ላይ የፕላንና ልማት ሚኒስቴርን ጠርቶ ይፋዊ ውይይት ማድረጉ ይታወሳል።

በዚህ ይፋዊ ውይይት ቋሚ ኮሚቴው ካስቀመጣቸው አቅጣጫዎች መካከል የፕላንና ልማት ሚኒስቴር፣ ከገንዘብ ሚኒስቴርና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ጋር የጋራ ውይይት አድርጎ የፕሮጀክቶቹ ግልጽ አመራር ማድረግ መሆኑ የሚታወስ ነው።

ይህ ውይይትም የክዋኔ ኦዲት ግኝቱን መሠረት በማድረግ የተወሰዱ የእርምት እርምጃዎችን ሪፖርት ለመገምገም የተዘጋጀ መድረክ መሆኑን የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ የሺመቤት ደምሴ (/) ገልፀዋል።

የእርምት እርምጃ ሪፖርቱን የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር / ፍፁም አሰፋ እና ሌሎች የስራ ኃላፊዎች እያቀረቡ ይገኛሉ።

‎( አለማየሁ ጌቴ)

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament

በዩቲዩብ

https://www.youtube.com/@FDREHOPR

በቴሌግራም

https://t.me/ParlamaNews

በትዊተር

http://twitter.com/fdrehopr

በዌብሳይት

www.hopr.gov.et ይከታተሉ።

 

‎የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በጋሞ ዞን በመሬት መንሸራተት አደጋ ለተጎዱ ዜጎች የ10 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በጋሞ ዞን በመሬት መንሸራተት አደጋ ለተጎዱ ዜጎች 10 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ

‎------------------------

‎(ዜና ፓርላማ) መጋቢት 25 2018 .ም፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በጋሞ ዞን በመሬት መንሸራተት አደጋ ሳቢያ ለተጎዱና ለተፈናቀሉ ወገኖች የሚውል 10 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል።

የምክር ቤቱ ምክትል አፈ-ጉባኤ የተከበሩ / ሎሚ በዶን ጨምሮ፣ የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር፣ የምክር ቤት አባላትና የጽሕፈት ቤት የሥራ ኃላፊዎች በዞኑ በአካል ተገኝተው የምክር ቤቱን አጋርነት አሳይተዋል።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ የተከበሩ ሎሚ በዶ፤ በዞኑ በተከሰተው አደጋ ምክንያት በወገኖቻችን ላይ በደረሰው ጉዳት እጅግ ማዘናቸውን ገልፀው ለተጎጂ ቤተሰቦች መፅናናትን ተመኝተዋል።

ምክር ቤቱ ያለውን አጋርነት ለማሳየትም 10 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ለጋሞ ዞን አስተዳደር ያስረከቡ ሲሆን ዜጎቸን በዘላቂነት ለማቋቋም በሚደረገው ተግባር ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡

የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምስ አድማሱ (/) ምክር ቤቱ ላሳየው ፈጣን ምላሽና አጋርነት በዞኑ ሕዝብና በአስተዳደሩ ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

እንዲህ ያሉ ድጋፎች የተረጂዎችን ሞራል ከመገንባት ባለፈ፣ መልሶ የማቋቋም ሥራውን እንደሚያቀላጥፉ ጠቁመዋል።

‎( አገሪቱ ጌቴ)

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament

በዩቲዩብ

https://www.youtube.com/@FDREHOPR

በቴሌግራም

https://t.me/ParlamaNews

በትዊተር

http://twitter.com/fdrehopr

በዌብሳይት

www.hopr.gov.et ይከታተሉ።

 

 

በጾታ
በፖለቲካ ፓርቲ

የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ሥልጣንና ተግባር:-

  • ሕግ ማውጣት፣
  • የፌደራል መንግስት በጀትን መርምሮ ማፅደቅ፣
  • መንግስታዊ አካላትን መከታተል፤ መቆጣጠር እና አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኝም እርምጃ መውሰድ፣
  • የራሱን የተለያዩ ኮሚቴዎችንና ሌሎች አስፈላጊ ክፍሎችን ማቋቋምና ማደራጀት፣
  • በራሱ የሚሰየሙ፣ የሚሾሙ እና የሚመረጡ የመንግስት ባለስልጣናትን መሰየም፣መሾም፣ማፅደቅና መምረጥ፣
  • አባላቱ ከመረጣቸው ህዝብ ጋር እንዲገናኙ  ማመቻቸት።

Image
📅

አዲስ መረሓ ግብር የለም

በአሁኑ ጊዜ ምንም የታቀዱ ዝግጅቶች የሉም።

የጽ/ቤቱ ተልዕኮ፣ ረዕይ እና ዕሴቶች

ተልዕኮ

ጽ/ቤቱ የም/ቤቱ አባላትና አካላት ለሚያከናውኗቸው የሕግ አወጣጥ፣ ክትትልና ቁጥጥር፣ የውክልና እንዲሁም የፓርላማ ዲፕሎማሲ ተግባራት የማማከር፣ የጥናትና ምርምር አስተዳደራዊ አገልግሎት መስጠት እና የመረጃ ተደራሽነትን ማረጋገጥ ነው።

ርዕይ

በ2022 ነፃ፣ ገለልተኛና ጥራት ያለው ሙያዊና አስተዳዳራዊ አገልግሎት የሚሰጥ ጽ/ቤት መሆን፣

የተቋሙ ዕሴቶች

  • ለጋራ ስኬት መቆም፣
  • ቀጣይነት ያለው ለውጥ፣
  • ግልፅነትና ተጠያቂነት፣
  • መከባበርና መተባበር፣
  • ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት፣
  • ታማኝነትና ቅንነት፣
  • ውሳኔ ሰጭነት እና
  • ብዙኃነት ናቸው፡፡