ምክር ቤቱ በአንቀጽ 55፣ አንቀጽ 70(1)፣ አንቀጽ 79(4)(ሐ)፣ አንቀጽ 82(2)(ሐ)፣ አንቀጽ 101፣ አንቀጽ 102፣ አንቀጽ 103 እና... የተሰጡት ሥልጣንና ተግባራት ይኖሩታል።
መረጃ ማቅረቢያ
መረጃ ማቅረቢያ ምንድነው?
መረጃ ማቅረቢያ ማለት ለምክር ቤቱ አስፈላጊ መረጃ ማቅረብ ማለት ነው። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቁጥጥርና የክትትል ስልጣኑን በተገቢው ለመፈጸም ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት መረጃ የሚሰበስብበት ስርዓት አለው።
ዓላማ፦
- የመንግስትና የህዝብ ሀብት በተገቢው መጠቀሙን ማረጋገጥ፤
- ስራዎች በህግና በስርዓት መፈጸማቸውን ማረጋገጥ፤
- ፍትሃዊና ፈጣን የልማት አቅጣጫ መኖሩን ማረጋገጥ፤
- ዴሞክራሲና መልካም አስተዳደርን ማረጋገጥ፤
- የዜጎች መብት፣ ሰላምና ጸጥታ መጠበቁን ማረጋገጥ።
ምክረ ሀሳብ የሚያቀርቡ አካላት
- የመንግስት አካላት
- ኮሚቴዎች
- ማህበረሰብ
- መንግስታዊ ያልሆኑ አካላት
ልዩ ልዩ ነጥቦች
- በመንግስት ወይም በህዝብ ጥቅም ላይ ጉዳት ሲደርስ፤
- ህገ መንግስቱ በአደጋ ላይ ነው ተብሎ ሲገመት፤
- የመንግስት ፖሊሲና ስትራቴጂ ሲደናቀፍ፤
- በህዝቦች መካከል ግጭት ሲኖር ወይም ሊፈጠር ሲችል፤
- የሰብዓዊ መብት ጥሰት ወይም ከፍተኛ የተፈጥሮ/ሰው ሰራሽ አደጋ ሲከሰት።
ውድቅ ሊያደርጉ የሚችሉ ጉዳዮች
- በፍርድ ቤት የተወሰኑ ወይም የተፈቱ ጉዳዮች፤
- በአስተዳደራዊ ወይም በፍትህ ሂደት የተፈቱ ጉዳዮች፤
- በህግ በተቋቋመ አካል የተመረመሩ ወይም የተወሰኑ ጉዳዮች፤
- መረጃው በቀጥታ ከራሱ ሳይሆን ከሌላ ሰው ብቻ የቀረበ ከሆነ።
ሚስጥራዊነት
- የመረጃ ሰጪው ማንነት በምክር ቤቱ፣ በአባላትና በቋሚ ኮሚቴዎች ሚስጥር ይጠበቃል።
- ምስክርነትና ሰነዶች ሚስጥር እንዲሆኑ ከተጠየቀ በሚስጥር ይጠበቃሉ።
- ለመረጃ ሰጪው ተገቢ የህግ ጥበቃ መኖሩ ይረጋገጣል።