ሚዲያ መግለጫ
------------------
ሰኔ 29 ቀን፣ 2018 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ማክሰኞ ሰኔ 30 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የመንግሥትን የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ለኢፌዴሪ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀርባሉ፡፡
በኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት አንቀፅ 55 ንዑስ አንቀፅ 17 እና በምክር ቤቱ የአሠራርና የአባላት የሥነ-ምግባር ደንብ ቁጥር 6/2008 አንቀፅ 81 ንዑስ አንቀፅ 1 እና 3 መሠረት የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትሩን እና ሌሎች የፌዴራሉ መንግሥት ባለስልጣናትን ለጥያቄ የመጥራትና የሕግ አስፈፃሚውን አካል አሠራር የመመርመር፣ የመከታተልና የመቆጣጠር ሥልጣን አለው፡፡
በዚሁ ሕገ መንግሥትና የምክር ቤቱ የአሠራርና የአባላት ሥነ-ምግባር ደንብ መሠረት 6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ ማክሰኞ ሰኔ 30 ቀን፣ 2018 ዓ.ም በሚያካሂደው 30ኛ መደበኛ ስብሰባው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በምክር ቤቱ ተገኝተው የመንግሥትን የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እና የ2019 በጀት ዓመት ዓመታዊ በጀት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ እንደሚሰጡ ይጠበቃል፡፡
በተያያዘም ምክር ቤቱ ፣ የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀትን አስመልክቶ የሚያቀርበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሃሳብ መርምሮ የበጀት አዋጁን እንደሚያፀደቅ ይጠበቃል፡፡
በስብሰባው ላይ ጥሪ የተደረገላቸው ተጋባዥ እንግዶች፣ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮችና የዓለም አቀፍ ተቋማት ተጠሪዎች፣ የሐይማኖት አባቶች፣ ታዋቂ ግለሰቦችና የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች የሚገኙ ሲሆን የጉባኤው ሙሉ ሂደትም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ በቀጥታ ሥርጭት የሚተላለፍ ይሆናል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament
በዩቲዩብ
https://www.youtube.com/@FDREHOPR
በቴሌግራም
https://t.me/ParlamaNews
በትዊተር
http://twitter.com/fdrehopr
በዌብሳይት
www.hopr.gov.et ይከታተሉ።
- መነሻ ገጽ
-
ያግኙን
እባኮትን ይህንን ቅጽ ይሙሉ እና የፓርላማ ጉብኝት መርሃ ግብር ለማዘጋጀት ያቅርቡፕሮስፔክተስ በቀላሉ መረጃ መስጠት ነው። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቁጥጥር እና የቁጥጥር ስልጣኑን ተግባራዊ ለማድረግ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት መረጃ የመሰብሰብ ስልቶችን አስቀምጧል።ያግኙን
-
ስብሰባዎች እና ዝግጅቶች
-
ተጨማሪ መረጃዎች
ምክር ቤቱ በአንቀጽ 55፣ አንቀጽ 70(1)፣ አንቀጽ 79(4)(ሐ)፣ አንቀጽ 82(2)(ሐ)፣ አንቀጽ 101፣ አንቀጽ 102፣ አንቀጽ 103 እና... የተሰጡት ሥልጣንና ተግባራት ይኖሩታል።
የኢ.ፌ.ድ.ሪ መርጃዎችን ያግኙ