"በኢትየጰያ አንፃራዊ ሰላም ተረጋግጧል" ----- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (/)

-------------

(ዜናፓርላማ) ሰኔ 30 2018 .ም፤ በኢትዮጵያ አንጻራዊ ሰላም መረጋገጡን የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አህመድ ገለጹ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይንን የገለጹት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሔደው 30 መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው የመንግስትን 2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም አስመልልቶ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት ነው፡፡

የምክር ቤት አባላት በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን ለማጽናትና የተጀመረውን አገራዊ ብልጽግና እውን ለማድረግ መንግስት ምን የመፍትሔ አማራጭ አስቀምጧል በሚል ጥያቄ አንሰተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (/ ) በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን ለማጽናት በተደረገው ሁለንተናዊ ጥረት አሁን ላይ መሻሻል እየታየ መሆኑን ገልጸው፤ ለአብነትም የብሔር እና የእርስ በርስ ግጭቶች መቀነሳቸውን አስገንዝበዋል፡፡

ኢትዮጵያ ሉዓላዊነቷን ለማስከበር እና ሰላሟን ለማጽናት በአስተማማኝ ቁመና ላይ እንደምትገኝ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒሰትሩ በታሪካዊ ጠላቶች ትዕዛዝ ሰጭነት የታጠቁ ሀይሎች እዚህም እዚያም ዓላማ የሌለው ግጭት ቢፈጥሩም የማይሳካላቸው እንደሆነ አስረድተዋል፡፡

የመንግስት እና የሀዝቡ ትስስር እያደገ በመጣ ቁጥር የኢትዮጵያ ተግዳሮቶች እየቀነሱ ይሄዳሉ፤ ይበልጥ ሰላምና መረጋጋት ይፈጠራል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ የታጠቁ ሀይሎች የሰላም አማራጭ እንዲቀበሉ የሚሰራው ስራ ተስፋ ሰጪ ውጤት እያመጣ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡

በተመሳሳይም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትግራይ ክልል ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ጊዜያዊ ክልላዊ መንግስት ከማቋቋም ባሻገር ዘርፈ-ብዙ ተግባራት የተከናወኑ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያን አንድነትና ሉዓላዊነት አደጋ ውስጥ የሚጥሉ ጥቃቶችን መመከት የሚያስችል ሀይል የተገነባ እንደሆነ የገለፁት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ኢትዮጵያውያን ለውጭ ጥቃት የማይንበረከኩ እንደሆኑ ከታሪካቸው መረዳት አንደሚቻል አስገንዝበዋል፡፡

ኢትዮጵያ አትወድቅም፤ የወደቁትንም ታነሳለች ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ፤ የብልጽግና ራዕይና ተልዕኮ ያልገባቸውን አካላት በማንቃት ለሀገራቸው እና ለህዝባቸው እድገት እንዲተጉ መንግስት በትኩረት አንደሚሰራ አስታውቀዋል፡፡

(በተስፋሁን ዋልተንጉስ)

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament

በዩቲዩብ

https://www.youtube.com/@FDREHOPR

በቴሌግራም

https://t.me/ParlamaNews

በትዊተር

http://twitter.com/fdrehopr

በዌብሳይት

www.hopr.gov.et ይከታተሉ።