(ዜና ፓርላማ) ህዳር 28 2014 /ም፤ 16ኛው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን "ወንድማማችነት ለህብረ ብሄራዊ አንድነት" በሚል መሪ ቃል በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተከብሯል።

የምክር ቤቱ /ቤት ዋና ፀሐፊ / ምስራቅ መኮንን የዘንድሮው የብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በሚከበርበት ወቅት በጠቅላይ ሚንስትር ዓቢይ አህመድ (/) የሚመራው ጥምር ኃይል ወራሪውን ኃይል በአፋር እና አማራ ክልል ወሮ ከያዘቸው ቦታዎች በአጭር ጊዜና በሚያስደንቅ ፍጥነት በማፅዳት የጀግንነት ግስገሴውን በቀጠለበት ወቅት መከበሩ የበዓሉን ድምቀት እጥፍ ድርብ ያደርገዋል ብለዋል

ወራሪው ኃይል ወሮ በያዛቸው የአማራ እና የአፋር አካባቢዎች ንጹሀንን ገድሏል፤ ሴቶችን ደፍሯል፤ የመንግሥትንና የግል ንብረቶችን ዘርፏል። ያሉ ሲሆን ይህንንም ወራሪ ኃይል ብዝሃነታችንን ጠብቀን እና አንድነታችንን አጠናክረን በማስወገድ የኢትዮጵያን ህልውና በፅኑ መሰረት ላይ ማስቀመጥ ይኖርብናል ሲሉም አክለው ተናግረዋል።

" ሕብረ-ብሔራዊ ፌደራላዊ ስርዓት ለሕብረ-ብሔራዊ አንድነት ያለው አስተዋጽኦ" በሚል ርዕስ የምክር ቤቱ /ቤት ምክትል ዋና ፀሀፊ ሄኖክ ስዩም (/) በፌዴሬሽን ምክር ቤት የተዘጋጀውን የውይይት መነሻ ፅሁፍ ለጽ/ቤቱ ሰራተኞች አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል።

መነሻ ጽሑፉ በቀጣይም በመላው ሀገሪቱ ውይይት እንደሚካሄድበትም ነው ከመድረኩ የተጠቆመው።

/ዋና ጸሀፊው ሄኖክ ስዩም (/) ባቀረቡት ጥናታዊ ፅሁፍ ለኢትዮጵያ ሕብረ ብሔራዊ የሆነ የፌደራል ስርዓት ዘርግቶ በተገቢው መንገድ መተግበር የቅንጦት ጉዳይ ሳይሆን ሁሉን የማሰባሰብና አገርን አንድ አድርጎ የማስቀጠል ጉዳይ እንደሆነ ገልፀው፤ ለብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች እንዲሁም ለቋንቋዎችና ሃይማኖቶች ተገቢውን እውቅና ለመስጠት የሚያስችል የፌደራሊዝም ስርአት መገንባትም ያስፈልጋል ነው ያሉት

በሚፍታህ ኪያር