የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ
null የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ
የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሚከተሉት ጉዳዮች ላይ ክትትልና ቁጥጥር ያከናውናል፡-
ሀ/ የፌደራል መንግሥቱ የፍትህ አስተዳደር ሕገ-መንግሥቱን መሠረት በማድረግ መደራጀቱንና በአግባቡ ተግባሩን እያከናወነ መሆኑን፤
ለ/ በሕገ-መንግሥቱ የተደነገጉ መብቶችና ነፃነቶች በአግባቡ መተግበራቸውን፤
ሐ/ ነፃና ፍትሃዊ የምርጫ ስርዓት መዘርጋቱን እና ሂደቱን፤
መ/ ሕብረተሰቡ ነፃ፣ ፍትሃዊና ቀልጣፋ የፍትህ አገልግሎት ማግኘቱን፤
ሠ/ ሙስናና ብልሹ አሠራርን መከላከልና መቆጣጠር የሚያስችል ሥርዓት በአግባቡ መዘርጋቱንና ሥራ ላይ መዋሉን፤
ረ/ በሕገ-መንግሥቱ አንቀፅ 54 (6) የተመለከተውን የህግ ከለላ የማንሳት እንዲሁም ሌሎች የአባላት መብትና ሥነ-ምግባር ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን፤
ሰ/ የወንጀል መከላከል ስራ በአግባቡ እየተከናወነ መሆኑን እንደዚሁም ለወንጀል ድርጊት ጠቋሚዎችና ምስክሮች በቂ ጥበቃ መደረጉን፤
ሸ/ የህዝብና የመንግስትን መብትና ጥቅም ለማስከበር የሚያስችል የህግ ምክር፣ ክስና ክርክር እየተካሄደ መሆኑን፤
ቀ/ በየደረጃው የሚገኙ የፌደራል መንግስት የዳኝነት አካላት በሕግ የተሰጣቸውን ተግባር እና ኃላፊነት በአግባቡ እየተወጡ መሆኑን፤
በ/ የመገናኛ Bzù¦N lxg¶tÜ Ä!äK‰s!ÃêE |R›T GNƬ½ s§M L¥T ybk#§cWN ¸Â XytÅwtÜ mçnùN፤
ተ/ የmNG|T mg¾ Bz#¦N ïRìC ytÈlÆcWN ¦§ðnT bxGÆb# መወጣታቸውን፤
ቸ/ የሚከታተላቸውና የሚቆጣጠራቸው ተቋማትን የሚመለከቱ ፖሊሲዎች፣ ህጎች፣ ስትራቴጂዎች እና ዕቅዶች በአግባቡ በሥራ ላይ መዋላቸውን ፤
ኅ/ የሚከታተላቸውና የሚቆጣጠራቸው ተቋማት የተመደበ ላቸውን በጀት በአግባቡና በውጤታማነት በስራ ላይ ማዋላቸውን፤
2/ የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ምክር ቤቱ ወደ ማንኛውም ቋሚ ኮሚቴ የሚመራውን ረቂቅ ህግ እና የሚቀርቡ የረቂቅ ህጎችን የረቂቅ ህግ አዘገጃጀት መርሆዎችን የተከተሉና የተሟሉ መሆናቸውን ይመረምራል፡፡
ተ.ቁ | የተቋሙ ስም |
1 | የፍትህ ሚኒስቴር እና ተጠሪ የሚደረጉለት ተቋማት፣ |
2 | ከአስፈፃሚ አካላት ውጪ ያሉ የዲሞክራሲ ተቋማት፣ |
3 | የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት እና ተጠሪ ተቋማት፣ |