null Banquet held at the Grand National palace in honor of the new Prime minster

ትናንት ማምሻውን በብሔራዊ ቤተ መንግስት በክቡር ፕሬዝዳንት / ሙላቱ ተሾመ ጋባዥነት ለአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዶክተር አብይ አሕመድ የእራት ግብዣ ተዘጋጅቷል፡፡ በእራት ግብዣው ስነ ስርዓት በርካታ ዲፕሎማቶች፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ የሃይማኖት አባቶች፣ አባጋዳዎች የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና ታዋቂ ግለሰቦች ባጠቃላይ 1500 በላይ የሚሆኑ የግብዣው ታዳሚ ሆነዋል፡፡ ፕሬዝዳንት / ሙላቱ ተሾመም ለታዳሚዎቹ ንግግር አድርገዋል፡፡