null The Second Phase Revitalization Forum on South Sudan

የውስጥና የውጭ አገር ቱሪስቶች ስለ አገሪቱ ታሪክና ባህል ግንዛቤ እንዲኖራቸው ቅርሶችን በቋሚና ጊዜያዊ ኤግዚቢሽን አደራጅቶ ለእይታ እንዲውሉ በታቀደው መሰረት ከአውሮፓ ህብረት የባህል ለልማት ፕሮጀክት ጋር በመተባበር የሰው ዘር ምንጭ ሙዝየም የህንፃ ዲዛይን ስራው ሰፊ ውይይት ተደርጎበት ርክክብ እንደተፈጸም ሚኒስትሯ ተናግረዋል፡፡

የሶስቱን አዋጆች መጽደቅ አስፈላጊነት በተመለከተ የውሳኔ ሃሳብና ሪፖርት ያቀረቡት  የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ጴጥሮስ ወልደ ሰንበት በአዋጆቹ ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ሰፊ ውይይት እንደተደረገባቸው ለምክር ቤቱ አብራርተዋል፡፡

የፀደቁት ረቂቅ አዋጆች የቤተሰብ ህግ አዋጅ ቁጥር 213/1992ን እንደገና ለማሻሻል፣ የፍትህ፣ የህግ ምርምርና ስልጠና ኢንስቲትዩት ለማቋቋም እንዲሁም የፌደራል ኤሌክትሮኒክ ፊርማ ለመደንገግ የቀረቡ ሲሆኑ፤ ም/ቤቱ ረቂቅ አዋጆቹን አስመልከቶ የቀረቡትን ሪፖርቶችና የውሳኔ ሃሳቦችን መርምሮ የቤተሰብ ህግ አዋጅ ቁጥር 213/1992ን በሶስት ድምጸ ተአቅቦ፣ በሶስት ተቃውሞ በአብላጫ ድምጽ አፅድቆታል፡፡

በሌላ በኩል ም/ቤቱ የፍትህ፣ የህግ ምርምርና ስልጠና ኢንስቲትዩትን ለማቋቋም እና የፌዴራል ኤሌክትሮኒክ ፊርማ ለመደንገግ የቀረቡትን ረቂቅ አዋጆችን ደግሞ በሙሉ ድምጽ አፅድቋቸዋል፡፡

በህገ-ወጥ መንገድ በግለሰቦች ሲዘዋወሩ የተገኙ 100 የብራና መጽሃፍትን እና 200 የኢትኖግራፊና ታሪካዊ ቅርሶችን ከፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን፣ ከገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ጋር በመተባበር ቅርሶቹ ወደ ባለስልጣኑ የቅርስ ስብስብ ክፍል ውስጥ እንዲገቡ መደረጋቸውንም አክለዋል፡፡

የውጭ ቱሪስት ፍሰት ጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣ ሲሆን በግማሽ ዓመት ውስጥ 485ሺህ 806 የውጭ ዜጎች አገሪቷን እንደጎበኙና ከዘርፉም 1 ቢሊየን 818 ሚሊየን 857 ሺህ 664 ዶላር ገቢ መገኘቱን ሚኒስትሯ በሪፖርታቸው ገልፀዋል፡፡