ምክር ቤቱ ሁለት ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መራ

(ዜና ፓርላማ) ግንቦት 19 2017 .ም፤ የሕዝብ ተወካዮች /ቤት ዛሬ ባካሄደው 32 መደበኛ ስብሰባ ሁለት ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ ለዝርዝር ዕይታ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መርቷል፡፡

በቀዳሚነት የተመራው የሥርዓተ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ ረቂቅ አዋጅ ሲሆን፤ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚንስትር የተከበሩ ተስፋዬ በልጂጌ (/) በረቂቅ አዋጁ ላይ የተዘጋጀውን አጭር ማብራሪያ አቅርበዋል፡፡

ኢትዮጵያ ተለያይነት ባላቸው ሥርዓተ ምህዳሮች የበለፀገች እና እነዚህ ሥርዓተ ምህዳሮች በሀገራዊ የልማት ጥረቶች ላይ ያላቸውን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና አካባቢያዊ አስተዋፅኦ ማሳደግ በማስፈለጉ የተዘጋጀ ረቂቅ አዋጅ እንደሆነ የተከበሩ ተስፋዬ (/) አስረድተዋል፡፡

እነዚህ ሥርዓተ-ምህዳሮች ዘላቂ ባልሆነ የተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀም ምክንያት በከፍተኛ ጫና ውስጥ በመሆናቸው ሥርዓተ ምህዳርን በዘላቂነት ለማስተዳደር የሚያስችል የሥርዓተ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ የህግ ማዕቀፍ ማስፈለጉን አንስተዋል፡፡

የፌደራል እና የክልል ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን ልዩ ፍላጎት እና ሁኔታ ከግምት ውስጥ ያስገባ የሥርዓተ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ የአሰራር ሥርዓቶችን መዘርጋት እንደሚገባም የተከበሩ ተስፋዬ (/) አብራርተዋል፡፡   

የምክር ቤቱ አባላት ረቂቅ አዋጁ የሚመራለት ቋሚ ኮሚቴ በጥልቀት ሊያየው ይገባል ያሉትን አስተያየት ካቀረቡ በኋላ፤ ረቂቅ አዋጁ ቁጥር 18/2017 ሆኖ ለዝርዝር ዕይታ በዋናነት ለውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢና አካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፣ በተባባሪነት ደግሞ የፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ተመርቷል፡፡

በቀጣይነት የተመራው የባለብዙ ተዋንያን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደርረቂቅ አዋጅ ሲሆን፤ የአዋጁ አስፈላጊነት ላይ በተከበሩ ተስፋዬ (/) አጭር ማብራሪያ ቀርቧል፡፡

በኢትዮጵያ የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎት፣ አስተዳደርና ልማት እንዲሁም በተፈጥሮ ሃብት ዘርፍ ያለውን የተደራሽነት፣ የጥራት፣ የአቅም እና የአፈጻጸም ውስንነትን ለመቅረፍ የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ ለማዘጋጀት የሚያግዝ አዋጅ እንደሆነ የመንግስት ተጠሪው አንስተዋል፡፡

በመንግሥት ብቻ ሲሰጥ የቆየውን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎት መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን፣ የግል ዘርፉን፣ የሕብረት ሥራ ማሕበራትን ወይም የሙያ ማሕበራትን በማቀናጀት ደረጃውን የጠበቀ፣ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የተደገፈ፣ ቀልጣፋ፣ ተደራሽ እና ተጠያቂነትን የሚያረጋግጥ የግብርና ኤክስቴንሽን የአገልግሎትና የአስተዳደር የሕግ ማዕቀፍ ማውጣት አስፈላጊ ስለመሆኑም አስረድተዋል፡፡

በመጨረሻም ረቂቅ አዋጁ ቁጥር 19/2017 ሆኖ ለዝርዝር ዕይታ ለግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሙሉ ድምጽ ተመርቷል፡፡