ምክር ቤቱ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሀገሪቱን የመጠጥ ውሃ ሽፋን ማሳደግ ላይ ትኩረት አድርጎ መስራት እንዳለበት ገለፀ

 (ዜና ፓርላማ) ግንቦት 19 ቀን 2017 . 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች /ቤት ባካሄደው 32 መደበኛ ስብሰባው የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የሀገሪቱን የመጠጥ ውሃ ሽፋን ማሳደግ ላይ ትኩረት አድርጎ መስራት እንዳለበት ገልጿል።

ምክር ቤቱ ባካደው መደበኛ ስብሰባው የምክር ቤት አባላት ለውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር / / ሀብታሙ ኢተፋ ላቀረቡት ጥያቄዎች ክቡር ሚንስትሩ የሰጡትን መልስና ማብራሪያ አዳምጧል።

የምክር ቤት አባላት ካቀረቧቸው ጥያቄዎች ውስጥ በዋና ዋና ከተሞች ጭምር የመጠጥ ውሃ አቅርቦት እጥረት መኖር፣ ውሃማ አካባቢዎች መጤ አረምን ጨምሮ ለብክለት መጋለጥ፣ በውሃ ጉድጓድ ቁፈራ፣ በውሃ ማስፋፊያ ፕሮጀክቶች መጓተትና ውጤት አልባ መሆን፣ በአዳዲስ የውሃ ፕሮጀክቶች ፍላጐት ላይ እና እንደ ሀገር የመጠጥ ውሃ ሽፋንን 100% ለማድረስ ምን እየተሰራ ነው የሚሉት በዋነኛነት ይገኙበታል።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር / / ሀብታሙ ኢተፋ ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡት ጥያቄዎች ምላሽ ሲሰጡ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሀገሪቱን የመጠጥ ውሃ ሽፋን ለማሳደግ በርካታ ስራዎችን መስራቱን አብራርተዋል።

ትልቁ ዓላማችን የተቀናጀ የውሃ ተፋሰስ ስራ ነው ያሉት ክቡር ሚንስትሩ፤ የውሃ ሽፋንን ለማሳደግ የከርሰ ምድርና የገፀ ምድር የውሃ መረጃ ወሳኝ ጉዳይ ነው። አሁን ላይ በሀገሪቱ ምን ያህል የውሃ አቅም እንዳለ መረጃ በማሰባሰብና በማደራጀት ረገድ ጥሩ ስራ ሰርተናል ብለዋል።

ክቡር ሚንስትሩ በአንዳንድ አካባቢዎች የመጠጥ ውሃ እጥረት ቢኖርም በበጀት አመቱ በሀገር ደረጃ 17 ሚሊየን ህዝብ ተጠቃሚ በማድረግ 76 በመቶ መድረስ መቻሉንም አመላክተዋል።

አያይዘውም .. 2030 የሀገሪቱን የውሃ ፍላጎት 100% ለማድረስ ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝና አሁን ላይ ባለው አፈፃፀምም ከአመት አመት በኋላ የታለመለት ግብ ላይ መድረስ እንደሚቻልም ነው ያብራሩት።

የታለመለት ግብ ላይ ለመድረስ የፌደራል መንግስት ከሚበጅተው በጀት በተጨማሪም ክልሎችም የበኩላቸውን ድጋፍ ማድረግ እንዳለባቸውም ነው ክቡር ሚንስትሩ ያስረዱት።

በመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች አፈፃጸምና ፍላጎቶች ዙሪያ ለቀረቡት ጥያቄዎች ሲመልሱ፤ ችግሮቹን ለመፍታት ጥረት እንደሚደረግ፣ በጀት የሚያስፈልጋቸው ተጠንተውና ተለይተው በበጀት እና በብድር እንዲሰሩ ትኩረት እንደሚደረግም ተናግረዋል።

በመጨረሻም በውሃ ዳርቻ የሚገኙ መጤ አረምንና ብክነትን በተመለከተም በቅርቡ በምክር ቤቱ የፀደቀው የውሃ አካል ዳርቻ አወሳሰን፣ ልማትና እንክብካቤ አዋጅ ብዙ ችግሮችን እንደሚፈታ ጠቁመው፤ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታትም ከባለ ሀብቶች ጋር በትብብር እና በመደጋገፍ  መስራት እንደሚገባ ገልፀዋል።