ምክር ቤቱ አቶ ተስፋዬ ንዋይን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አድርጎ ሾመ
(ዜና ፓርላማ) ሰኔ 05 ፣ 2017 ዓ.ም.፤ አዲስ አበባ፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቶ ተስፋዬ ንዋይን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አድርጎ ሾሟል፡፡
በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ( ዶ/ር) የቀረበውን የዕጩዎች ሹመት ውሳኔ ሃሳብ የመንግሰት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር የተከበሩ ተስፋዬ በልጅጌ ( ዶ/ር) ያቀረቡ ሲሆን፣ የምርጫ ሂደቱ ብዝሃነትን ያማከለ እና የማንኛውም ፖለቲካ ፓርቲ አባል ያልሆኑ መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡
በተጨማሪም ምክር ቤቱ አቶ ተክሊት ይመስል እና ወ/ሮ ነሲም አሊን የቦርዱ አመራሮች እንዲሆኑ ሾሟል፡፡
ተሿሚዎቹ በምክር ቤቱ ፊት ቀርበው ቃለ-መሃላ የፈጸሙ ሲሆን፣ ምክር ቤቱ ሹመቱን በሁለት ድምጸ- ተዓቅቦ እና በአብላጫ ድምጽ አጽድቆታል፡፡