ምክር ቤቱ አቶ ተስፋዬ ንዋይን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አድርጎ ሾመ

(ዜና ፓርላማ) ሰኔ 05 2017 .. አዲስ አበባ፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቶ ተስፋዬ ንዋይን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አድርጎ ሾሟል፡፡

በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ( /) የቀረበውን የዕጩዎች ሹመት ውሳኔ ሃሳብ የመንግሰት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር የተከበሩ ተስፋዬ በልጅጌ ( /) ያቀረቡ ሲሆን፣  የምርጫ ሂደቱ ብዝሃነትን ያማከለ እና የማንኛውም ፖለቲካ ፓርቲ አባል  ያልሆኑ መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡

በተጨማሪም ምክር ቤቱ አቶ ተክሊት ይመስል እና / ነሲም አሊን የቦርዱ አመራሮች እንዲሆኑ ሾሟል፡፡

ተሿሚዎቹ በምክር ቤቱ ፊት ቀርበው ቃለ-መሃላ የፈጸሙ ሲሆን፣ ምክር ቤቱ ሹመቱን በሁለት ድምጸ- ተዓቅቦ እና በአብላጫ ድምጽ አጽድቆታል፡፡