ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ረቂቅ አዋጅን መርምሮ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መራ

 (ዜና ፓርላማ) ሰኔ 5 2017 .ም፤ የኢትዮጵያ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ረቂቅ አዋጅ ማብራሪያን የመንግሰት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር የተከበሩ ተስፋዬ በልጅጌ ( /) አቅርበዋል፡፡

የተከበሩ ተስፋዬ በማብራሪያቸውም፣ ረቂቁ ዜጎቻችን በውጭ ሀገር ለስራ ሲሰማሩ መብታቸው፣ ጥቅማቸው እና ክብራቸው ተጠብቆ እንዲሰሩ የሚያስችል መሆኑን አስረድተዋል፡፡

የምክር ቤት አባላት በበኩላቸው፣ ረቂቅ አዋጁ ዜጎች የሰሩት ሃብት እና ንብረት ባለቤት እንዲሆኑ፣ ክብራቸው እና ጥቅማቸው እንዲከበር የሚያስችል በመሆኑ የረቂቁን አስፈላጊነት አብራርተዋል፡፡

በአንጻሩ፣ ረቂቁ የሚመራለት ቋሚ ኮሚቴ ዜጎች ለስራ ስምሪት ወደ ውጭ ሃገር ሲሰማሩ የአለምን የስራ እድል ፈጠራ ታሳቢ ያደረገ የቴክኖሎጂ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ማብቃት፣ ኤጄንሲዎች በጉዳዩ ዙሪያ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ማወያየት፣ ዜጎች ወደ ውጭ ሀገር ከመሄዳቸው በፊት ስለሚሄዱበት ሀገር ግንዛቤ እንዲኖራቸው ስልጠና እንዲሰጣቸው እና በየሀገሩ ያሉ ኤምባሲዎች የዜጎች ክብር እና ጥቅም ተጠብቆ እንዲሰሩ በትኩረት መስራት እንደሚጋባ አሳስበዋል፡፡

እንዲሁም በህክምና፣ ምህንድስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ እና በፋይናንስ ዘርፎች ተመርቀው የተቀመጡ በርካታ ዜጎች ስላሉ የሚመራለት ቋሚ ኮሚቴ ይህንኑ ግምት ውስጥ በማስገባት እንዲሰራ አባላቱ ጨምረው አሳስበዋል፡፡

ምክር ቤቱም ረቂቁን ለሰው ሃብት ልማት፣ ስራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ለዝርዝር ዕይታ በሙሉ ድምጽ  መርቶታል፡፡