ምክር ቤቱ የዕፅዋት ጥበቃና ኳራንታይን ረቂቅ አዋጅን ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መርቷል፡
(ዜና ፓርላማ) ሰኔ 5 ፣ 2017 ዓ.ም፤ የረቂቁን ማብራሪያ የመንግሰት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር የተከበሩ ተስፋዬ በልጅጌ ( ዶ/ር) ያቀረቡ ሲሆን፣ ረቂቁ የዘመናዊ የዕፅዋት ጥበቃ እና ኳራንታይን ለማዘመን፣ መጤ እና ወራሪ ተባዮችን ለመከላከል፣ በዘርፉ ማሕበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ረቂቁ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው አብራርተዋል፡፡
የምክር ቤት አባሉ የተከበሩ ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) የሚመራለት ቋሚ ኮሚቴ ወራሪ ተክሎች በተለይም በተለምዶ እምቦጭ የተባለው መጤ ተክል እያደረሰ ያለውን ጉዳት ግምት ውስጥ አስገብቶ ሊሰራ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡
ረቂቅ አዋጁ ለዝርዝር ዕይታ ለግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሙሉ ድምጽ ተመርቷል፡፡