የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎችን የያዘ ቡድን ነገ በጅግጅጋ ከተማ በሚካሄደው ሕዝባዊ የውይይት መድረክ ላይ ለመሳተፍ ጂግጂጋ ከተማ ገብቷል።

ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎቹ ጅግጅጋ ገራድ ዊል ዋል አየር ማረፊያ ሲደርሱ በክልሉ የሥራ ኀላፊዎች ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።