(ዜና ፓርላማ) ታህሳስ 25/2014 .ም፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን እጩ ኮሚሽነሮች አቀራረብ ስርዓት በኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች /ቤት ስለመዘርጋቱ አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ተናግረዋል፡፡

የእጩ ኮሚሽነሮችን ጥቆማ የሚቀበልና የሚያደራጅ የጥቆማ ተቀባይ ኮሚቴ የተቋቋመ ሲሆን፤ የእጩ ኮሚሽነሮችን ጥቆማ ከመቀበል ጀምሮ በም/ቤቱ ቀርበው እስከሚሾሙበት ድረስ የተለያዩ ተግባራትን እንደሚያከናውንና የኮሚቴው ሰብሳቢም ሄኖክ ስዩም (/) እና ሌሎች ሁለት አባላትም መካተታቸውን የተከበሩ አፈ ጉባኤ አስታውቀዋል፡፡

የምክክር ኮሚሽኑን እጩ ኮሚሽነሮች ጥቆማ አቀባበል አሳታፊ፣ ግልጽ፣ ታኣማኒና ከአድሎ የጸዳ እንዲሆን ለማስቻል የሚያግዝ የአማካሪ ቡድንም ተቋቁሟል፡፡

የአማካሪ ቡድኑ በተከበሩ አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ የሚመራ ሲሆን፤ የፌዴሬሽን /ቤት አፈ ጉባኤ፣ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዘዳንት፣ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ተወካይ እንዲሁም የሲቪክ ማህበራት ጥምረት ተወካይ በአባልነት ተካተውበታል፡፡

አማካሪ ቡድኑ የተለያዩ ተግባርና ኃላፊነት የተሰጡት ሲሆን፤ ከቀረቡ እጩዎች ውስጥ በአዋጁ ላይ የተቀመጡትን መስፈርቶች በከፍተኛ ደረጃ የሚያሟሉትን እጩዎች በመለየት ረገድ አፈ ጉባኤውን ማማከር ዋነኛው ስለመሆኑ ዛሬ በተደረገው ውይይት ተጠቁሟል፡፡

የጥቆማ መስጫ መርሃ ግብርና ጥቆማ የሚሰጥበት ፎርማት ገና ይፋ ሳይደረግ ጥቆማዎች እየቀረቡ ስለመሆኑ አፈ ጉባኤው ገልጸው፤ ነገር ግን እነዚህ ጥቆማዎች ተቀባይነት እንደማይኖራቸው አስታውቀዋል፡፡

ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን እጩ ኮሚሽነሮች ማቅረቢያ ጊዜ፣ ፎርማትና አጠቃላይ የእጩዎች አቀራረብ ስርዓትን በተመለከተ አፈ-ጉባኤው ዛሬ ከሰአት በኋላ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጡ ይጠበቃል፡፡

አበባው ዮሴፍ