የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አመራሮች የሞሮኮ አፈ-ጉባኤን በቦሌ አየር ማረፊያ ተገኝተው ተቀበሉ
(ዜና ፓርላማ)፤ ጥቅምት 19፣ 2015 ዓ.ም፤ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሠላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሞሮኮ አፈ-ጉባኤን በቦሌ አየር ማረፊያ ተገኝተው ተቀብለዋል።
የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ የተከበሩ ዶ/ር ፈቲህ ማህዲ እና የውጭ ግንኙነት ንዑስ ኮሚቴ ተወካይ የተከበሩ አምባሳደር ዶ/ር ቶፊቅ አብዱላሂ ዛሬ ጠዋት በቦሌ አየር ማረፊያ ተገኝተው የሞሮኮ አፈ-ጉባኤ ሚስተር ራቺድ ታልቢ ኤል አል አላሚን ተቀብለዋል፡፡
የሞሮኮ አፈ-ጉባኤ ወደ ኢትዮጵያ የመጡት ለቀድሞው የሞሮኮ ንጉስ ሀሰን II (ሁለተኛ) የሚበረከተውን የፓን አፍሪካ አዋርድ (Pan African Award) ሽልማት ለመቀበል በወቅቱ የሞሮኮ ንጉስ ሞሀመድ IV (አራተኛ) ተወክለው መሆኑ ታውቋል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት
በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament
በዩቲዩብ https://www.youtube.com/watch?v=cp_8F5TEeFE
በቴሌግራም https://t.me/ParlamaNews
በትዊተር http://twitter.com/fdrehopr
በዌብሳይት www.hopr.gov.et ይከታተሉ
Copyright 2020 - All rights reserved. House of Peoples' Representatives
Sign In