የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጽህፈት ቤት
የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጽህፈት ቤት የተቋቋመበት ዓላማ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሕገመንግስታዊ ተልዕኮውን ለማሳካት የሚያስፈልጉ ሙያዊ ድጋፍና አስተዳደራዊ አገልግሎቶችን ለመስጠት ነው
ጽህፈት ቤቱ የሚከተሉት ስልጣን እና ተግባራት ይኖሩታል፦
፩/ ለምክር ቤቱ ህግ አወጣጥ፣ ክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም ለውክልና ስራ የሚያስፈልጉ ሙያዊ ድጋፍና አስተዳደራዊ አገልግሎቶችን ይሰጣል፤
፪/ ለምክር ቤቱና ምክር ቤቱ ለሚያቋቁማቸው ኮሚቴዎችና ሌሎች ውስጣዊ አካላት አጠቃላይ ሙያዊና አስተዳደራዊ አገልግሎት ይሰጣል፤
፫/ የፌደራል ነጋሪት ጋዜጣን ያስተዳድራል፤
፬/ የምክር ቤቱን የህዝብ ግንኙነት ተግባራት ያከናውናል፤
፭/ ተቋማዊ ቀጣይነትን ያረጋግጣል፤
፮/ ለምክር ቤቱ አባላት እና አካላት በህግ የተወሰኑ ጥቅማጥቅሞችን እና ልዩ መብቶችን ያስፈጽማል፤
፯/ የምክር ቤት አባላት መኖሪያ ቤቶችን ያስተዳድራል፣ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመመካከር ፀጥታና ደህንነት መከበሩን ይከታተላል፤ በማንኛውም የምክር ቤቱ ቅጥር ግቢ ፀጥታና ስነስርዓት መከበሩን ያረጋግጣል፤
፰/ የምክር ቤቱን በጀት ያዘጋጃል፤
፱/ ለምክር ቤቱ አካላትና አባላት የቤተ መጽሃፍት፣ የምርምር፤ የመረጃ እና ዶክሜንቴሽን አገልግሎት ይሰጣል፤
፲/ የአቅም ግንባታ ስራዎችን ይሰራል፤
፲፩/ ለምክር ቤቱና ለምክር ቤቱ የተለያዩ አካላት የቃለጉባኤ፤ የአዳራሽ አገልግሎት፤ የህትመትና ሌሎች የኮንፈረንስ አገልግሎቶች ይሰጣል፤
፲፪/ ለምክር ቤቱ አባላትና አካላት የትራንስፖርት አገልግሎት ይሰጣል፤
፲፫/ የንብረት ባለቤት ይሆናል፣ ውል ይዋዋላል፣ በስሙ ይከሳል፣ ይከሰሳል፤
፲፬/ ዓላማውን ለማሳካት የሚረዱ ሌሎች ተዛማጅ ተግባራትን ያከናውናል።
Copyright 2020 - All rights reserved. House of Peoples' Representatives