የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ አፈጻጸም 80 በመቶ መድረሱ ህዝቡ ላይ መነቃቃት እንደሚፈጥር ተገለጸ

(ዜና ፓርላማ)፤ ግንቦት 18 ቀን 2013 .ም፤ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተፈጥሮ ሃብት፣ መስኖና ኢነርጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ አፈጻጸም 80 በመቶ መድረሱ  ህዝቡ ላይ መነቃቃት እንደሚፈጥር ገልጿል፡፡

ቋሚ ኮሚቴው ይህን ያለው በዛሬው እለት የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴርንና የተጠሪ ተቋማቱን የዘጠኝ ወራት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት በገመገመበት ወቅት ነው ፡፡

ግንባታው ሂደት የነበሩ የአፈጻጸም ችግሮችን በመፍታት 80 በመቶ መድረሱን በጥንካሬ ያነሱት የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ ፈቲያ የሱፍ ሂደቱ ሕዝቡ ላይ የሞራል መነቃቃት የሚፈጥር ነው ሲሉም ጠቅሰዋል፡፡

በፋይናንስበፐብሊክ ዲፕሎማሲውም ረገድ ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸው  የግንባታው አፈጻጸም ቀጣይነት እዲንኖረው እንዳስቻሉም ወ/ሮ ፈቲያ አክለው አብራርተዋል ፡፡ 

በተቋሙ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነትን ለማስፋት እየተሰሩ ያሉ ስራዎች አበረታች ቢሆኑም ከካሳ ክፍያና ከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ብረቶች ስርቆት ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት ከክልሎችና ከሕዝቡ ጋር በትብብር መስራት እንዳለበትም ወ/ሮ ፈቲያ አሳስበዋል፡፡

ለገጠር ከተሞች የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግና የኃይል ብክነትን መከላከል የሚያስችሉ ስራዎች ላይ በትኩረት መሰራት እንዳለበትም ነው ሰብሳቢዋ የጠቆሙት፡፡

በምግብ ራስንመቻልና ከውጭ የሚገባን ስንዴ ለማስቀረት የመስኖ ልማት  ስረዎችም ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ወ/ሮ ፈቲሃ ጠቅሰዋል፡፡

የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር /ር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ በበኩላቸው  የመስኖ ልማት ስራዎችን አስመልክተው በአሁኑ ወቅት ስራ ላይ የሚገኙ አራት እንዲሁም አዳዲስ ወደ ስራ የገቡ ስምንት በድምሩ አስራ ሁለት የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች መኖራቸውን ተናግረዋል፡፡  

ሚኒስትሩ በሪፖርታቸው ባለፉት ሁለትና ሶስት አመታት ከ 16 ሚሊዮን ሕዝብ በላይ የንጹህ መጠት ውሃ አቅርቦት እንዲያገኝ መደረጉንም አብራርተዋል፡፡ 

በደርብ ሙሉዬ