(ዜና ፓርላማ) ታህሳስ 21/2014 .ም፤ የአገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች በህዝብ እንደሚመረጡና ሹመታቸው በህዝብ ተወካዮች /ቤት እንደሚጸድቅ የህግ፣ ፍትህና ዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል፡፡

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ / እፀገነት መንግስቱ በጋዜጣዊ መግለጫው እንዳሳወቁት የኮሚሽነሮች ጥቆማ መላውን የኢትዮጵያ ህዝብ ያካተተ ሲሆን፤ ከተጠቆሙት 14 እጩዎች መካከል 11 ተመልምለው በአፈ ጉባኤው አቅራቢነት በም/ቤቱ የሚሾሙበት አሰራር ተዘርግቷል፡፡

ኮሚሽነሮቹ በም/ቤቱ ከተሰየሙበት እለት ጀምሮ 3 ዓመታት የሚቆይ የስራ ጊዜ የሚኖራቸው ሲሆን፤ እንደ አስፈላጊነቱ ቆይታቸው ሊራዘም እንደሚችልም ተገልጿል፡፡

በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ ስለ ድርድር የሚገልጽ ምንም አይነት ይዘት አለመካተቱን ሰብሳቢዋ ጠቁመው፤ የአዋጁ ዋና አላማ እስካሁን መግባባት ላይ ያልተደረሰባቸውና የኢትዮጵያን ህልውና የሚፈታተኑ የተለያዩ አገራዊ ጉዳዮች ላይ መላውን የኢትዮጵያ ህዝብ ያካተተ ውይይት በማድረግ ችግሮችን መፍታት እንደሆነ አመላክተዋል፡፡

የሚቋቋመው ኮሚሽን ከምክክር መድረኮቹ የሚያገኘውን ምክረ ሀሳብ በመቀመር ተግባራዊ እንዲደረጉ እንደሚሰራ ጠቁመው፤ /ቤቱን ጨምሮ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ኃላፊነት ወስደው እንደሚያስፈጽሙና ለስኬታማነቱም ጠንካራ የክትትልና ቁጥጥር ስርዓት እንደሚዘረጋ ሰብሳቢዋ ተናግረዋል፡፡

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ትላንት ባካሄደው 2 ልዩ ስብሰባው ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ለማቋቋም የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ በአብላጫ ድምጽ ስለማጽደቁ መዘገባችን ይታወሳል፡፡

አበባው ዮሴፍ