የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአዲስ አበባ ከተማ ለሚገኙ ተባባሪ አካላት ዛሬ ስልጠና መስጠት ጀምሯል
ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከየወረዳው ለተውጣጡ 713 ሰልጣኞች በግዮን ሆቴል እየተሰጠ የሚገኘው ይህ ስልጠና፤ ተባባሪ አካላቱ በየወረዳቸው የሚገኙ ተሳታፊዎችን በመለየት ሂደት ውስጥ ለኮሚሽኑ እገዛ እንዲያደርጉ አቅማቸውን ለማጎልበት ታስቦ ነው፡፡
በተጨማሪም በስልጠናው መርሃ ግብር መሰረት ዛሬ እየተሰጠ ያለው ስልጠና ተባባሪ አካላቱ በሀገራዊ ምክክር ሂደት ላይ መሰረታዊ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ያለመ ነው፡፡
ስልጠናው በሀገራዊ ምክክር ፅንሰ ሀሳብ እና ምንነት እንዲሁም ስለኮሚሽኑ ዓለማ፣ ተግባራትና እና የወደፊት አቅጣጫዎች ትኩረት የሚያደርግ መሆኑን ከኮሚሽኑ የማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament
በዩቲዩብ https://www.youtube.com/@FDREHOPR
በቴሌግራም https://t.me/ParlamaNews
በትዊተር http://twitter.com/fdrehopr
በዌብሳይት www.hopr.gov.et ይከታተሉ።
Copyright 2020 - All rights reserved. House of Peoples' Representatives
Sign In