የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጽ/ቤት ዋና ፀሓፊ

ዶ/ር ምስራቅ መኮንን

  • የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጽ/ቤት ዋና ፀሓፊ
  • Telephone: +251-011-1-24 10 15
  • Mobile: +251-911 52 62 97
  • Email: mismek@gmail.com
  • Personal Website: #
    • Follow:

Biography

ዶ/ር ምስራቅ መኮንን የትነበርክ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የእንስሳት ሐኪምና ክፍል ኃላፊ ሆነው አገልግለዋል፡፡ በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በደቡብ ወሎ አስተዳደር የዞን ስራ አስፈፃሚ አባል በመሆን አገልግለዋል፡፡ የአማራ ክልል ምክር ቤት ምክትል አፈጉባኤና አፈጉባኤ በመሆን ሰርተዋል፡፡ የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር እና የእንስሳትና የዓሣ ሀብት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ ሆነው አገልግለዋል፡፡ እ.ኤ.አ. ከጁን8/ 2018 ጀምሮ በኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፅሕፈት ቤት ዋና ጸሐፊ ሆነው እያገለገሉ ይገኛሉ፡፡

በሀረር ከተማ የተወለዱት ዶ/ር መስራቅ DVM ዲግሪ በእንስሳት ሕክምና ከሃቫና የግብርና እና የእንስሳት ሳይንስ ተቋም (ከኩዩባ ሪፑብሊክ)፣ የማስተርስ ዲግሪ (MA) in Transformational Leadership and Change from Greenwich University (UK) ምሩቅ ናቸው፡፡

በተጨማሪም በእንግሊዝ ሀገር ከበርሚንግሃም ዩኒቨርሲቲ የዲሞክራሲ፣ የሕግ የበላይነት እና የደህንነት ስልጠና የወሰዱ ሲሆን በኢትዮጵያ ውስጥ የማህበረሰብ ውይይት ስልጠናን ለመምራት በወሰዱት ስልጠና የብቃት ማረጋገጫ አላቸው ፡፡

የአማራ መልሶ መቋቋምና ልማት ድርጅት (አመልድ) ሊቀመንበር በመሆን ያገለገሉት ዶ/ር ምስራቅ፤ የአራቱ የፌደራል ሆስፒታሎች ስራአስፈፃሚ ቦርድ አባል፣ የቅዱስጴጥሮስ ሪፈራል ሆስፒታል የስራአስፈፃሚ ቦርድ ሊቀመንበር፤ የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት የስራ አስፈፃሚ ቦርድ አባል እና የብሔራዊ ፀረ HIV/ADS ሕብረት ለሴቶች (National Coalition for Women against HIV/AIDS)   በመሆን አገልግለዋል፡፡ በተጨማሪም እና ብሔራዊ የኢትዮጵያ ትምህርት ቤቶች ምገባ ተነሳሽነት ኢንስቲትዩት (the day Ethiopian school meal initiative institute)  የቦርድ አባል ናቸው፡፡