Government Allocates 500 Million Birr
null Government Allocates 500 Million Birr
Portal Admin
Modified 6 Years ago.
የሶስቱን አዋጆች መጽደቅ አስፈላጊነት በተመለከተ የውሳኔ ሃሳብና ሪፖርት ያቀረቡት የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ጴጥሮስ ወልደ ሰንበት በአዋጆቹ ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ሰፊ ውይይት እንደተደረገባቸው ለምክር ቤቱ አብራርተዋል፡፡
የፀደቁት ረቂቅ አዋጆች የቤተሰብ ህግ አዋጅ ቁጥር 213/1992ን እንደገና ለማሻሻል፣ የፍትህ፣ የህግ ምርምርና ስልጠና ኢንስቲትዩት ለማቋቋም እንዲሁም የፌደራል ኤሌክትሮኒክ ፊርማ ለመደንገግ የቀረቡ ሲሆኑ፤ ም/ቤቱ ረቂቅ አዋጆቹን አስመልከቶ የቀረቡትን ሪፖርቶችና የውሳኔ ሃሳቦችን መርምሮ የቤተሰብ ህግ አዋጅ ቁጥር 213/1992ን በሶስት ድምጸ ተአቅቦ፣ በሶስት ተቃውሞ በአብላጫ ድምጽ አፅድቆታል፡፡
በሌላ በኩል ም/ቤቱ የፍትህ፣ የህግ ምርምርና ስልጠና ኢንስቲትዩትን ለማቋቋም እና የፌዴራል ኤሌክትሮኒክ ፊርማ ለመደንገግ የቀረቡትን ረቂቅ አዋጆችን ደግሞ በሙሉ ድምጽ አፅድቋቸዋል፡፡