null Revitalization talks underway

ዲዛይን ስራው ሰፊ ውይይት ተደርጎበት ርክክብ እንደተፈጸም ሚኒስትሯ ተናግረዋል፡፡ በህገ-ወጥ መንገድ በግለሰቦች ሲዘዋወሩ የተገኙ 100 የብራና መጽሃፍትን እና 200 የኢትኖግራፊና ታሪካዊ ቅርሶችን ከፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን፣ ከገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ጋር በመተባበር ቅርሶቹ ወደ ባለስልጣኑ የቅርስ ስብስብ ክፍል ውስጥ እንዲገቡ መደረጋቸውንም አክለዋል፡፡

የኢፌዴሪ ባህልና ቱሪዝም ሚንስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ሂሩት ወልደማሪያም እንደገለጹት ቅርሶች በተፈጥሮ፣ በእድሜ ብዛት እና በሰው ሰራሽ አደጋዎች ጉዳት እንዳይደርስባቸው በግማሽ ዓመቱ ለ10 ቅርሶች የጥበቃና እንክብካቤ ስራዎች ለማከናወን በታቀደው መሰረት ለ10ም ቅርሶች ጥበቃና እንክብካቤ ማድረግ ተችሏል ብለዋል፡፡

የውስጥና የውጭ አገር ቱሪስቶች ስለ አገሪቱ ታሪክና ባህል ግንዛቤ እንዲኖራቸው ቅርሶችን በቋሚና ጊዜያዊ ኤግዚቢሽን አደራጅቶ ለእይታ እንዲውሉ በታቀደው መሰረት ከአውሮፓ ህብረት የባህል ለልማት ፕሮጀክት ጋር በመተባበር የሰው ዘር ምንጭ ሙዝየም የህንፃ ዲዛይን ስራው ሰፊ ውይይት ተደርጎበት ርክክብ እንደተፈጸም ሚኒስትሯ ተናግረዋል፡፡

የውጭ ቱሪስት ፍሰት ጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣ ሲሆን በግማሽ ዓመት ውስጥ 485ሺህ 806 የውጭ ዜጎች አገሪቷን እንደጎበኙና ከዘርፉም 1 ቢሊየን 818 ሚሊየን 857 ሺህ 664 ዶላር ገቢ መገኘቱን ሚኒስትሯ በሪፖርታቸው ገልፀዋል፡፡