null Committee urges the Ministry of Culture and Tourism

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በሰጡት ምላሽ ችግሩን ለመቅረፍ የተደረገው እንቅስቃሴ ከችግሩ ውስብስብነት አንጻር ሲታይ ውስንነት እንዳለበት ጠቁመው፤ ለግጭቱ መከሰት መንስኤው በየደረጃው የሚገኙ የአመራሮች የመወሰን አቅም ውስነነት እንደሆነ አስረድተዋል፡፡ 

በውይይቱም ግጭቱ በተነሳበት ወቅት መንግስት አፋጣኝ ርምጃ ከመውሰድ ለምን እንደተቆጠበ፣ የሱፐርቪዥኑ ሪፖርት መዘግየቱንና ግጭቱ የተከሰተባቸውን ሁሉንም ቦታዎች የዳሰሰ አለመሆኑ የምክር ቤት አባላት ጥያቄዎችን አንስተዋል፡፡

የግጭቱ መነሻ በህዝቦች መካከል የተፈጠረ አለመሆኑ ከሁለቱም ክልል ተፈናቃይ ዜጎች በተሰጠ አስተያየት መረዳት የተቻለ ሲሆን፣ ለዜጎች መፈናቀልና ህይወት መጥፋት መንስኤው ህዝቡ ሳይሆን መሬትን መሰረት ያደረገ የኪራይ ሰብሳቢው ፍላጎትና ያለአግባብ ልጠቀም የሚል አጀንዳ እና በ1997 ዓ.ም የተካሄደውን ህዝበ ውሳኔ መሰረት አድርጎ የሁለቱ ክልሎች የወሰን ማካለል ስራውና የህግ የበላይነትን የማስከበር ተግባሩ በወቅቱ አለመፈጸም ግጭቱን እንዳባበሰው ተገልጿል፡፡

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በሰጡት ምላሽ ችግሩን ለመቅረፍ የተደረገው እንቅስቃሴ ከችግሩ ውስብስብነት አንጻር ሲታይ ውስንነት እንዳለበት ጠቁመው፤ ለግጭቱ መከሰት መንስኤው በየደረጃው የሚገኙ የአመራሮች የመወሰን አቅም ውስነነት እንደሆነ አስረድተዋል፡፡