null The House of People's Representatives evaluated the performance of the 2019 budget plan of the House.

ዜና ፓርላማ 02/11/2012 ዓ፡- የህዝብ ተወካዩች ም/ቤት የ2ዐ11 በጀት አመት እቅድ አፈፃፀምን ገመገመ፡፡

ም/ቤቱ በበጀት አመቱ የታቀዱ ግቦችንና የተከናወኑ ተግባራትን አንደሁም ያጋጠሙ ተግዳሮቶችንና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ላይ በማተኮር ሠፊ ውይይት አድርጓል፡፡

በመላው ሃገሪቱ የተጀመረውን ሪፎርም ተከትሎ የፌዴራል መንግስት የአስፈፃሚ አካላትን ሥልጣንና አደረጃጀት ማሻሻያ የተደረገ በመሆኑ ቋሚ ኮሚቴዎችን በአደስ መልክ በማደራጀት የተቋማቱን ሥልጣንና ተግባራ የሚመጥን ክትትልና ግመገማ በማድረግ ውጤት ተመዝግቧል፡፡

ም/ቤቱ በበጀት አመቱ 6ዐ አዋጆችንና 2 ደንቦችን ያፀደቀ ሲሆን 32 ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡ ከፌደሬሽን ም/ቤት ጋር በጋራ በተሠጠው ሥልጣን መሠረትም 2 ውሳኔዎችን በጋራ ማስተላለፉን ከቀረበው ሪፖርት መረዳት ተችሏል፡፡

በሪፖርቱ በተጠናቀቀው በጀት አመት የፓርላመንቲዊ የአሠራር ስርዓትን ተግባራዊነት ለማረጋገጥ የሚያስችል አቅም በማጐለበት የህዝብ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ተችሏል ነው የተባለው፡፡

በዚህም ከሃገራት ጋር ያለውን ወዳጅነትና ትብብር የሚያጠናክሩ፣ የዜጐችን ዴሞክራሲና የመደራጀት መብት የሚያጐለብቱ፣ ብሔራዊ መግባባትና እርቅ አንዲሠፍን የሚያደርጉና ሌሎች ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማጐልበት የሚያስችሉ አስተዎፆዎችን ሊያበረክቱ የሚችሉ ህጐችን አውጥቷል፡፡

የሃገሪቱን ብሔራዎ ጥቅም የሚያስከብሩና ለመንግስት እቅድ አፈፃፀም ድጋፍ የሚያስገኝ የፓርላማ  ዲኘሎማሲ የመፈፀም አቅምን ለማሣደግ በተሠራው ሥራ የሃገሪቱን የሪፎርም እንቅስቃሴ የሚያንፀባርቅ አንደነበረም ሪፖርቱ አመላክቷል፡፡

በበጀት አመቱ ቋሚ ኮሚቴዎች የ1ዐዐ ቀን ወይም  የአንድ ገፅ እቅድ እንዲሁም አመታዊ የተቋማት ዕቅዶችን በመገምገም ግብረ-መልሶችን መስጠት ተችሏል፡፡

ተቁማት ከሚያቀርቡት እቅድ በመነሳትም ጉድሎቶችን በመለየት ማስተካከያ እንዲያደርጉ አቅጣጫ በማመላከት እና ተቀባይነት የሌላቸው አቅዶችን ውድቅ በማድረግ የሚፈፀምና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ በሚያርግ መልኩ አንደያቅዱም ተደርጓል፡፡

የጠቅላይ ሚኒስትሩና የሚንስትሮች የጥያቄ ጊዜ በአቅድ የተያዘ ቢሆንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከተገኙበት አንድ የጥያቄ ጊዜ ውጪ አለመደረጉ እንደክፍፍተት በሪፖርቱ የተካተተ ሲሆን በቃጣይ ሊታረም እንደሚገባም አቅጣጫ ተቀመጧል፡፡

በበጀት አመቱ  የመሠረተ ልማት ግንባታዎች አፈፃፀም መዘግየትና የጥራት ችግር፣ የፓርኮችና ቱሪዝም መዳረሻዎች ጉዳት መድረስ፣ የብርዕ፣የጥራጥሬ፣ የቅባትና የቅመማቅመም ሰብሎች ምርታማነትን ለማሳደግ የተሠራው  ሥራ ዝቅተኛ መሆን እንዲሁም በአንደንድ ዩኒቨርስቲዎች  የመማር ማስተማሩ ሂደት በፀጥታ ችግር መስተጓጐሉ በምቤቱ አባላት ክትትልና ቁጥጥር የተለዩ ዋና ዋና ችግሮች ነበሩ፡፡

የምርጫ ክልል ግንኙነት አሠራርን በማሻሻል ለህዝቡ ወቅታዊ የሆነ መረጃ አና ምላሽ አሠጣጥን በማሳደግ የህዝብ  ውክልና አፈፃፀም ሥራ  ከቀደመው ጊዜ የተሻለ ቢሆንም ቀሪ ትግባራት እንዳለ በሪፖርቱ ተመላክቷል፡፡

ሪፖርቱ ከተደመጠ በኃላ ም/ቤቱ በተጠናቀቀው በጀት አመት   የም/ቤት አባላት የመኖሪያ ቤት  እደላና ጥገና ፍትሃዊ አለመሆን፣ የህክምና አገልግሎት አሠጣጥ ቀልጣፍ አለመሆን ፣ የትራንስፖርት አገልግሎት ምቹ አለመሆን እንዲሁም የመስክ ሥራ ለመሥራት የሚከፈለው የውሎ አበል በቂ አለመሆን ከም/ቤት አባላት የተነሱ  ጥያቄዎች ነበሩ፡፡

የም/ቤቱን አፈ ጉባኤን ጨምሮ ሌሎች ሃላፊዎች በሰጡት ምላሽ ከአባላት አገልግሎት አሠጣጥ ጋር የተነሱ ችግሮች በ2ዐ12 ዓ/ም ለመቅረፍም ከስምምነት ላይ ተደርሶ የበጀት አመቱ እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ተጠናቋል፡፡