null The House of Peoples' Representatives in its 45th regular session held on June 18, 2019, approved the appointment of the Ethiopian News Agency Board mebers.

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሰኔ 11 ቀን 2011 ባካሄደው 45ኛ መደበኛ ስብሰባው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት የቦርድ አባላትን ሹመት መርምሮ አጸደቀ፣

በዚህም መሰረት፡-

  1. አቶ ታዜር ገ/እግዚአብሄር በርሄን የቦርዱ ሰብሳቢ
  2. ወ/ሮ ህይወት ኃይሉ አላኮን              አባል
  3. አቶ አብነት ዘርፉ አብርሃምን               “
  4. አቶ ታምራት ኃይሌ ደገፋን /ፒኤችዲ/        “
  5. አቶ መኩሪያ መካሻን /ረዳት ፕሮፌሰር/        “
  6. አቶ መሱድ አደም ሽፋን                    “
  7. አቶ በቀለ ሙለታ ቶላን                     “

አድርጎ የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት የላከውን የቦርድ አባላት ዝርዝርና የትምህርት ዝግጅት ከመረመረ በኋላ ምክር ቤቱ ሹመቱን በሙሉ ድምጽ ያጸደቀ ሲሆን ተሹዋሚዎቹም በምክር ቤቱ ፊት ቀርበው ከሃገሪቱና ከህዝቡ የተሰጠንን ሃላፊነት በቅንነትና በታማኝነት እንወጣለን ሲሉ በጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዘዳንቷ ክብርት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ አማካኝነት ቃለ-መሃላ ፈጽመዋል፡፡