ይሳተፉ

በወንጀል የተገኘ ንብረት ህጋዊ ማስመሰልና ሽብርተኝነትን በገንዘብ የመርዳት ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የቀረበ ረ

በወንጀል የተገኘ ንብረት ህጋዊ ማስመሰል እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ወንጀል የደህንነት ስጋት ከመሆኑ በተጨማሪ የፋይናንስ ሥርዓቱ የተረጋጋ፣ ግልጸኝነት ያለው፣ ጤናማና ቀልጣፋ እንዳይሆን የሚያደርግ በመሆኑ፤
ከዚህ ቀደም የነበረው አዋጅ ቁጥር 780/2013 ግልጽነት የጎደለው እና በተግባር ችግር የፈጠረ በመሆኑ ከሌሎች ህጎች ጋር የማይጣጣምና ወቅታዊ ለሆኑ ችግሮች በቂ ምላሽ የማይሰጥ ሆኖ በመገኘቱ በአዲስና በተሟላ የሕግ ማዕቀፍ መተካት በማስፈለጉ፤
በወንጀል የተገኘ ንብረት ህጋዊ ማስመሰል እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ወንጀልን ለመዋጋት በዓለም አቀፍ ደረጃ ጥረት እየተደረገ በመሆኑና ኢትዮጵያም የዚህ ዓለም አቀፍ ጥረት አካል በመሆኗ እና ይህንን በስራ ላይ ማዋል በማስፈለጉ፤
በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ህገ መንግስት አንቀጽ 55 (1) መሰረት የሚከተለው ታወጇል፡፡

ይምረጡ