ይሳተፉ

የፌደራል የፍትህና የሕግ ኢንስቲትዩትን እንደገና ለማቋቋም የወጣ አዋጅ

የፌዴራል ፍትህና ሕግ ኢንስቲትዩት የሚሰጣቸው ስልጠናዎች እና ሌሎች የሚያከናውናቸው ተግባራት ለዳኝነት እና የፍትህ አካላት ቢሆንም ተጠሪነቱ አስፈፃሚ አካሉ ጋር መሆኑ የዳኝነት አካሉን ፍላጎት በአግባቡ አሟልቶ ሥራውን ከመምራት እንፃር ክፍተት የሚታይ ከመሆኑም በተጨማሪ የዳኝነቱን አካሉን ነፃነትና እና ገለልተኝነት ጥያቄ ውስጥ የሚስገባ ሆኖ በመገኘቱ፤ ተጠሪነቱ ለዳኝነት አካሉ የሆነ፣ ስራውን በአግባቡ ለማከናወን የሚስችል የሰው ሀይል እና የአሰራር አደረጃጀት ያለው የፍትህና ሕግ ተቋም በማቋቋም በእውቀቱ፣ በክህሎቱ፣ በአመለካከቱ፣ እንዲሁም በሥነ-ምግባሩ ብቁ የሆነና የተሟላ ስብዕና ያለው የዳኝነት እና የፍትህ አካላት አመራር እና ባለሙያ ማፍራት ለፍትህ ስርዓቱ ውጤታማነት እጅግ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤ ሕጎችን ከወቅታዊ የአገሪቱ የዕድገት ደረጃ ጋር የተጣጣሙ ለማድረግ እንዲሁም የዳኝነት፣ የፍትህ አካላትና ሌሎች ከፍትህና ሕግ ሥራ ጋር ግንኙነት ያላቸው አካላትን ቀልጣፋ፣ ውጤታማና ተደራሽ ለማድረግ ጥናትና ምርምሮችን ማከናወን አስፈላጊ በመሆኑ፤ የአገሪቱ የፍትህ ዘርፍ የተሰጠውን ተልዕኮ በብቃት እያሳካ ስለመሆን አለመሆኑ የሚያሳይ አስተማማኝና የተሟላ የፍትህና ሕግ መረጃ ለመሰብሰብ እና ለማደራጀት የሚችል በቂ የሰው ሀይል እና አግባብነት ያለው የአሰራር እና አአደረጃጀት ሥርዓት ያለው ተቋም ማቋቋም አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤ በፍትህ ሥርዓቱና በሕግ ትምህርት ቤቶች ተግባራዊ የሚደረጉ የማሻሻያ ሥራዎችን በተቀናጀ መልኩ ለመምራትና ለማስፈጸም የሚያስችል አሰራር መዘርጋት አስፈላጊ በመሆኑ፤

ይምረጡ