ይሳተፉ

የኢትዮጵያ የተመሰከረላቸው የሂሣብ ባለሙያዎች ኢንስቲትዩት ረቂቅ አዋጅ

በመንግስት እና በግሉ ዘርፍ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሪፖርት እና የኦዲት ደረጃዎች እንዲተገበሩ መንግስት የወሰነ በመሆኑ ይህንን ለማስፈፀም በቂ እና ብቁ የተመሰከረላቸው የሒሳብ ባለሙያዎች ማፍራት በማስፈለጉ፤
የተመሰከረላቸው የሒሳብ ባለሙያዎች ለማፍራት እና ሙያውን ለማሳደግ ተቋም ማቋቋም በማስፈለጉ፤
የሒሳብ ሙያን እና የሒሳብ ባለሙያን በሀገር እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚወክል ተቋም በማስፈለጉ፤
የሕዝብ ጥቅምን ለማስጠበቅ የሒሳብ ሙያን እና የሙያተኛውን አቅም ማሳደግ በማስፈለጉ፤

ይምረጡ