"ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት)" እና "ሸኔ" በሽብርተኝነት ተፈረጁ
5ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 6ኛ ዓመት የስራ ዘመን 13ኛ መደበኛ ስብሰባ በመካሄድ ላይ ነው፡፡
ም/ቤቱ ዛሬ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ በሚያካሄደው 13ኛ መደበኛ ስብሰባ "ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት)" እና "ሸኔ" በሽብርተኝነት እንዲሰየሙ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ያቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ ም/ቤቱ በአንድ ደምፅ ተአቅቦ በአብላጫ ድምፅ አጹድቋል፡፡