ምክር ቤቱ ለ2014 በጀት ዓመት በቀረበው የበጀት ዝርዝር መግለጫ ላይ ተወያየ

(ዜና ፓርላማ)፣ ሰኔ 8 ቀን 2013 .ም፣ አዲስ አበባ፤ የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች /ቤት ዛሬ ባካሄደው 15 መደበኛ ጉባኤው በ2014 በጀት ዓመት አጠቃላይ የበጀት ዝርዝር መግለጫ ላይ ተወያይቷል፡፡

ምክር ቤቱ የገንዘብ ሚኒስትሩ ክቡር አቶ አህመድ ሽዴ ለ2014 በጀት አመት ያቀረቡትን ዝርዝር የበጀት መግለጫ ካዳመጠ በኋላ የተመደበው በጀት ለታለመለት ዓላማ እንዲውል በፕሮግራም በጀት አጠቃቀም ላይ ልዩ ክትትል መድረግ እንዳለበት አሳስቧል፡፡

የምክር ቤቱ አባላት አክለውም የተመደበውን በጀት በአግባቡ ጥቅም ላይ ለማዋልና ኢኮኖሚውን ለማሳደግ መንግሥት በአገሪቱ እየተከሰተ ያለውን የዋጋ ንረት መቆጣጣር እንዳለበት አስታውሰው ይህን ማድረግ ካልተቻለ የዋጋ ንረቱ ወደ ነጠላ አኃዝ ከመውረድ ይልቅ ሊጨምር እንደሚችል ሥጋታቸውን ገልፀዋል፡፡

ምክር ቤቱ በቀረበው የበጀት መግለጫ ላይ በጥልቀት ከተወያየ በኋላ ረቂቅ የበጀት አዋጁን ለዝርዝር እይታ ለገቢ፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ መርቷል፡፡

ለ2014 በጀት አመት ብር 561.7 አጠቃላይ ወጪ በጀት የተመደበ ሲሆን ከዚህ ውስጥ ለመደበኛ ወጪ ብር 162.2፣ ለካፒታል ወጪ መሸፈኛ ብር 183.5 ቢሊዮን፣ ለክልል መንግሥታት የበጀት ድጋፍ ብር 204 ቢሊዮን እና ለዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈፀሚያ ብር 12 ቢሊዮን ተደግፎ እንደቀረበ የገንዘብ ሚንስትሩ ክቡር አቶ አህመድ ሽዴ ለምክር ቤቱ አስረድተዋል፡፡

ሚኒስትሩ አያይዘውም የፕሮግራም በጀት አጠቃቀምን ለማጠናከር በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በኩል ክትትል እንደሚደረግ እና የግብርና ምርቶችን በማሳደግና የንግድ ሥርዓቱን በማዘመን በአገሪቱ እየተከሰተ ያለውን የዋጋ ንረት ለመከላከል እየተሰራ መሆኑን ነው ለምክር ቤት አባላት ያብራሩት፡፡

በመጨረሻም ባለበጀት መስሪያ ቤቶች የተመደበላቸውን በጀት ለታለመለት ዓላማ በቁጠባና በውጤታማነት ጥቅም ላይ ማዋል እንዳለባቸው ነው የገንዘብ ሚንስትሩ ያሳሰቡት፡፡

በጋሹ  ይግዛው