null Irish government to support Ethiopian parliament detailed reform program.

የህዝብ ተወካዮች ምር ቤት አፈጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ ከአየርላንድ አምባሳደር ሶኒያ ሃይላንድ ጋር ቀጣይ የፓርላማ አሰራር ሊያዘምኑ በሚችሉ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት ተስማሙ፡፡

አቶ ታገሰ ጫፎ ስምምነቱ ፓርላማን ለማዘመን በተደረገ ጥናት መሰረት የተሻለ ተሞክሮ ያለቸውን አገራት በማሳተፍ ቀጣይ የፓርላማ ስራውን ለማዘመን  እና  ህዝቡ የሚፈልገውን የዳበረ የፖለቲካ ምህዳርን ለማሳለጥ በሚያግዙ ጉዳዮች ላይ ከፍተኛ ትኩረት ለመስጠት ታስቦ እደሆነ ነው የገለጹት፡፡

ፓርላማው በሚሰራቸው በተለይ ህግን የማውጣት፣ የክትትልና ቁጥጥር ስራ እንዲሁም የህዝብ ውክልና ስራዎች ላይ ከዚህ ቀደም ሲከተላቸው የነበሩ አሰራሮች ቢኖሩትም በአሁኑ ወቅት እየመጣ ካለው አጠቃላይ አገራዊ ለውጥ ጋር ለማስኬድ አዳዲስ ስራዎችን ማካተት አስፈላጊ በመሆኑ ከተለያዩ ዩኒቨርትሲዎችና ከባለሙያዎች የተወጣጣ  ቡድን እንደተቋቋመ  ነው አፈ-ጉባዔው የጠቆሙት፡፡

አፈ-ጉባዔው አክለውም ለተጀመረው ሪፎርም የሚያስፈልጉ ጉዳዮች በጥናት ተለይተው ቋሚ ኮሚቴዎች ተወያይተውባቸው የዕቅድ መርሐ ግብር የወጣለት ሲሆን ስራውም የባለሙያዎችንና የሌሎች አገራትን ተሞክሮ እንዲሁም የገንዘብ ድጋፍ የሚጠይቅ በመሆኑ ለአለም አቀፍ ማህበረሰብ በተደረገው ጥሪ መሰረት መጀመሪያ የመጣው የአየርላን መንግስት እንደሆነ ተናግረው በቀጣይ የሚመጣውን  ገንዘብም ሆነ የግብዓት አቅርቦት በዕቅዱ መሰረት የሚመራ  እንደሆነም አንስተዋል፡፡

 የአየርላንድ አምባሳደር ሲኒያ ሃይላንድ በበኩላቸው ዛሬ የተደረገው ስምምነት ውጤታማ የሆነ የፓርላማ ስርዓትን ለመገንባት ኢትዮጵያ ባደረገቸው ጥሪ መሰረት እንደሆነ አስታውሰው፡ ፓርላማው ባወጣው ፕሮግራም መሰረት የፓርላማውን አቅም ለማጎልበት  ትኩረት በመስጠት በብቃት እንዲሰራ ለማድረግ የበኩላቸውን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን ነው የገለጹት፡፡

አምባሳደር ሶኒያ አክለውም በዋናነት በአሁኑ ወቅት በሃገሪቱ እየመጣ ባለው የዴሞክራሲ ባህ
ል መጐለበትና  በሁሉም ዘርፍ እየመጣ ባለው ዕድገት የፓርላማው ድርሻው የጎላ በመሆኑ ይህም ለድጋፍ እዳነሳሳቸው ነው ያብራሩት፡፡

በመጨረሻም አፈ-ጉባዔው የዲሞክራሲ ምህዳሩ ሲሰፋ በዛው ልክ በህዝቡ ዘንድ የሚነሱ የተለያዩ ጉዳዮች ተገቢውን ትኩረት በማግኘት እልባት የሚሰጥበት ፓርላማውም የህዝብ ውክልና ስራ እና የውይይት አድማሱን የሚያሰፋበት እንዲሆን በቀጣይም ሌሎች አገራትም በጥናቱ መሰረት በወጡ ፕሮግራሞች ተሳትፈው ፓርላማውን ለማዘመን እንደሚሰሩ ጠቁመዋል፡፡