null The House elected its new speaker.

ምክር ቤቱ  ባካሄደው 3ኛ መደበኛ ስብሰባው አቶ ታገሰ ጫፎን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አድርጎ መረጧል፤

ጥቅምት 8/2011 ዓ.ም. ፤ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔነት በእጩነት ቀርበው የተመረጡት አቶ ታገሰ ጫፎ በምክር ቤቱ ፊት ቀርበው ቃለ መሃላ ፈፅመዋል።

ከቃለ መሃላው በኋላም ተሰናባቿ አፈጉባዔ ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል እና ተመራጩ አፈጉባዔ አቶ ታገሰ ጫፎ የስልጣን ርክክብ አድርገዋል።

አዲስ የተሾሙት አፈ-ጉባኤ የአቶ ታገሰ ጫፎ የትምህርት ዝግጅትና የስራ ልድም ለምክር ቤቱ ተዘርዝሯል፡፡

ምክር ቤቱን ለላፉት ወራት በአፈ ጉባኤነት ሲያገለግሉ የነበሩት ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል በዚህ ሳምንት ያቀረቡትን መልቀቂያ ምክር ቤቱ መቀበሉ ይታወሳል።

መልቀቂያውን ተከትሎም ወይዘሮ ሙፈሪያት አዲስ ለተቋቋመው የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር በመሆን በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ መሾማቸው ይታወሳል።