null የገቢ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ

የገቢ ፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሚከተሉት ጉዳዮች ክትትልና ቁጥጥር ያከናውናል፡-

  1. የአገሪቱን የገንዘብእና የኢኮኖሚ ልማትና ትብብር ተግባራት በአግባቡ እየተከናወኑ መሆናቸውን፤
  2. የፌደራል መንግስት ታክስና ቀረጥ አስተዳደር እንዲሁም የመንግስት ገቢ አሰባሰብ በአግባቡ እየተከናወነ መሆኑን፤
  3. የፌደራል መንግሥት ዓመታዊና ተጨማሪ በጀት በአግባቡ ተዘጋጅቶ  መቅረቡን እና መጽደቁን፤
  4. ለክልሎች የሚሰጥ ድጎማ በቀመሩ መሠረት መጽደቁን፤
  5. የፌደራል መንግስት ፋይናንስ እናንብረት አስተዳደር በአግባቡ መከናወኑን እናውጤታማ መሆኑን፤
  6. የአገሪቱን የኢኮኖሚ ዕድገት ቀጣይነት እና ፍትሃዊነት እንዲሁም የተረጋጋ  የማክሮ ኢኮኖሚ ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ፓሊሲዎች መመንጨታቸውን እና በአግባቡ ስራ ላይ መዋላቸውን፣ ኢኮኖሚው በተገቢው መንገድ እየተመራ መሆኑን፤
  7. የአገሪቱ የልማት እቅድ እና የልማት ፕሮጀክቶች የአዘገጃጀትና አፈፃፀም ስርዓት  መዘርጋቱን እንዲሁም በወቅቱ በስራ ላይ መዋሉን፤
  8. የአገሪቱ የስነ-ህዝብ ፓሊሲ መዘጋጀቱን፣ የማክሮ - ኢኮኖሚና የፊስካል ፖሊሲዎች  መመንጨታቸውን እና በትክክል በስራ ላይ መዋላቸውን፤
  9. ትክክለኛ የሆነ የመንግስት የበጀት፣ የሂሳብ አያያዝ፣ የክፍያና የውስጥ ኦዲት ስርዓት መዘርጋቱንና በአግባቡ   እየተፈፀመ መሆኑን፤
  10. የኢኮኖሚ ትብብሮችና ትስስሮች ከመደረጋቸው በፊት በአገሪቱ የኢኮኖሚ አፈፃፀም ላይ የሚያስከትሉት ውጤት የሚፈተሽ እና የሚገመገም መሆኑን፤
  11. በመንግስት የኢኮኖሚና የፋይናንስ ፖሊሲ መሠረት የመንግስት የልማት ድርጅቶች በአገሪቱ የኢኮኖሚና ንግድ እንቅስቃሴ ገንቢ ሚና እያበረከቱ መሆኑን፤
  12. የመንግስት የልማት ድርጅቶች የስራ እንቅስቃሴ ትርፋማነትና የቴክኖሎጂ ሽግግርን የሚያረጋግጥ መሆኑን፤
  13. የመንግስት የልማት ድርጅቶች በህግ የተሰጣቸውን ተግባር በአግባቡ እየተገበሩ መሆኑን፤
  14. የመንግስት የልማት ድርጅቶች ውጤታማ በሆነ መንገድ መመራታቸውንና በአግባቡ ወደ ግል ይዞታ የተዛወሩ መሆናቸውን፤
  15. የመንግስት የልማት ድርጅቶች የሚሰጡት የህዝብ አገልግሎት በአግባቡ መከናወኑን እና የውስጥና የውጭ መልካም አስተዳደር ጉዳዮች በተመለከተ፤
  16. የመንግስት የልማት ድርጅቶች አነስተኛና ጥቃቅን ተቋማትን ጨምሮ በልማት ለሚሳተፉ ሌሎች ተቋማት የሚያደርጉት ድጋፍ።
  17. የሚከታተላቸውና የሚቆጣጠራቸው ተቋማትን የሚመለከቱ ፖሊሲዎች፣ ህጎች፣  ስትራቴጂዎች  እና እቅዶች በአግባቡ በሥራ ላይ መዋላቸውን፤
  18. የሚከታተላቸውና የሚቆጣጠራቸው ተቋማት የተመደበላቸውን በጀት በአግባቡና በውጤታማነት በስራ ላይ ማዋላቸውን፡፡

ተ.ቁ

የተጠሪ መስሪያቤቶች ስም ዝርዝር

1

የገንዘብ ሚኒስቴር

2

የገቢዎች ሚኒስቴር

3

ፕላን እና ልማት ኮሚሽን

4

የማዕከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ

5

የፓሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት

6

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ

7

የመንግስት ግዢና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት

8

የኢትዮጵያ የሂሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድ

9

የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር

10

የመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ኤጀንሲ

11

የመንግስት ግዢና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ

12

የጉምሩክ ኮሚሽን

የኮሚቴ አባላት