(ዜና ፓርላማ) ሰኔ 10 ቀን፣ 2017 ዓ.ም፤ ምክር ቤቱ ባካሄደው ጉባኤ የስታርትአፕ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መርቷል።
ረቂቅ አዋጁን አስመልክቶ የመንግሰት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር የተከበሩ ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) ለምክር ቤቱ ማብራሪያ አቅርበዋል፡፡
በማብራሪያቸውም ረቂቅ አዋጁ ኢኖቬሽን ነባር አሠራሮችን፣ የምርትና የአገልግሎት ሂደቶችንና ምርቶችን በሳይንሳዊ መንገድ በመቀየር ሰዎች ሕይወታቸውን በተሻለ መንገድ እንዲመሩ የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ሀገራት ይህን ከባቢያዊ ሥርዓት ለመፍጠር የሚያስችሉ ሕጎች ማውጣታቸውን እና በዚህ ዘርፍ ከተሰማሩ ከሃሳብ አፍላቂዎች ጀምሮ መዋዕለ ንዋያቸውን ኢንቨስት ላደረጉና ለሚያደርጉ ግለሰቦችና ድርጅቶች የአገራቱ አቅም የሚፈቅደውን እና ተገቢ ነው ያሉትን የማበረታቻ ማዕቀፍ አዘጋጅተው ወደ ሥራ ማስገባታቸውንም አብራርተዋል፡፡
በአገራችን ኢትዮጵያ ይህን ሥርዓት መፍጠር ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂን ከማስረጽና በኢኮኖሚው ውስጥ ሊያመጣ የሚችለውን አዎንታዊ ውጤት የሚመጣ፣ በተለይም ለወጣቶች የሥራ ዕድል የመፍጠር አቅሙም ከፍተኛ የሆነ እንዲሁም በአገር የኢኮኖሚ ዕድገት ላይ ሊያመጣ የሚችለውን ለውጥ ታሳቢ በማድረግ የሕግ ማዕቀፍ ለመፍጠር አስፈላጊ መሆኑንም ነው የተከበሩ ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) የገለጹት።
የምክር ቤት አባላት በበኩላቸው ረቂቅ አዋጁ ሀሳብን ወደ ገንዘብ የሚቀየርበትን መንገድ የሚፈጥር እና ፈጠራን የሚያበረታታ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ምክር ቤቱ በረቂቅ አዋጁ ላይ በስፋት ከተወያየበት በኋላ ረቂቅ አዋጅ ቁጥር 2320/2017 ሆኖ ለዝርዝር ዕይታ ለሰው ሃብት ልማት፣ ስራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሙሉ ድምጽ መርቷል፡፡
- መነሻ ገጽ
-
ያግኙን
ምክር ቤቱ በአንቀጽ 55፣ አንቀጽ 70(1)፣ አንቀጽ 79(4)(ሐ)፣ አንቀጽ 82(2)(ሐ)፣ አንቀጽ 101፣ አንቀጽ 102፣ አንቀጽ 103 እና... የተሰጡት ሥልጣንና ተግባራት ይኖሩታል።እባኮትን ይህንን ቅጽ ይሙሉ እና የፓርላማ ጉብኝት መርሃ ግብር ለማዘጋጀት ያቅርቡፕሮስፔክተስ በቀላሉ መረጃ መስጠት ነው። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቁጥጥር እና የቁጥጥር ስልጣኑን ተግባራዊ ለማድረግ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት መረጃ የመሰብሰብ ስልቶችን አስቀምጧል።ምክር ቤቱ በአንቀጽ 55፣ አንቀጽ 70(1)፣ አንቀጽ 79(4)(ሐ)፣ አንቀጽ 82(2)(ሐ)፣ አንቀጽ 101፣ አንቀጽ 102፣ አንቀጽ 103 እና... የተሰጡት ሥልጣንና ተግባራት ይኖሩታል።የምክር ቤቱ የአሰራርና የአባላት ሥነ ምግባር ቁጥር 6/2008 አንቀጽ 105 የሹመት ዓይነቶች በሦስት የተከፈሉ መሆናቸውን ያመለክታል።
-
ስብሰባዎች እና ዝግጅቶች
ቀጣይ መርሓ ግብሮች
አዲስ መረሓ ግብር የለም -
የእውቀት መረጃዎች
የኢ.ፌ.ድ.ሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት
ተጨማሪ ለማንበብ...የኢትዮጵያ ፓርላማ የተቋቋመው በህዳር 3 ቀን 1931 ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ በሐምሌ ወር 1931 የመጀመሪያውን ሕገ መንግሥት ካወጁ በኋላ ነው። እንደዚያም ሆኖ አሠራሩ እንደየአገዛዙ ይለያያል። ይህ ጽሑፍ በ... የገቡትን ፓርላማዎች ምንነት ለማቅረብ ይሞክራል።
የኢ.ፌ.ድ.ሪ መርጃዎችን ያግኙ